Tuesday, August 6, 2013

በስብሰባ ተወጥሮ ያደረው ወያኔ መስማማት ተስኖታል::

በስብሰባ ተወጥሮ ያደረው ወያኔ መስማማት ተስኖታል:: አደርባዮች እና የድል አጥቢያ አርበኞች ጨንቋቸዋል::
ከየተኛው ወገንእንደሚለጠፉ ግራ ገብቷቸዋል::
 የደህንነት እና የህወሓት ወታደራዊው ክንፍ በተጠንቀቅ ላይ ነው:: ባለስልጣናቱ ከውጪውአለም እየተደረገባቸውን
ጫና እና ግፊት በፍጹም አንቀበለም የሚል ድምዳሜ ላይ ለመድረስ እርስ በእርስ ሲላተሙአድረዋል::
ሃገራችን የጥበበኛ ህዝቦች እና የጥበበኛ መሪዎች ሃገርየምትሆንበትን ጊዜ የምንፈልግ እኛ ለውጥ ፈላጊ ልጆቿዛሬ
 ላይን ተቀምጠን ትላንትን የምንመኝ ለነገውትውልድ
 የማናስብ በፍርሃት ድባብ ተውጠን ስደትንእና ገንዝእብን የምናሳድድ መሆናችን በመታወቁበስልጣን ላይ ያለው
መንግስት ስልጣኑንን እንዴትአስረዝሞ ሃገር ወዳድ የሆኑ
ጠላት የሚላቸውንኢትዮጵያውያንን ነቃቅሎ የሚያጠፋበት ስልትበቡድናዊ አምባገነንነት እየዶለተ እና በስልጣን
 ሽኩቻእርስ በእርሱ እየተባላ ባለበት ወቅት እኛ አንድነት
አጥተል በጋራ ዘመም በቀኝ አክራሪ እና ባፈጀ ባረጀየፖለቲካ ግራውንድ እየተሽከረከርን ህዝብዊመቆላለፍን
 ልንፈጥር አለመቻላችን ለአገዛዙ አመቺአድርጎታል::
 እስኪ የወያኔን ስጋት ያነቡ
ዘንድ ጋብዘናል::
ከትላንት ሃምሌ 28 ሊነጋ የተበተነው የወያነው የውጥረት ስብሰባ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ነበረ ለሊቱን
የተጓዘው:: እንደቀድሞው እቅዳችን ትራንስፎርሜሽናችን  ልማታችን ምናምናችን ዲሞክራሲያችን ሰላማችን የጼረ
 ህዝቦቻችን…ምናምን የሚል አልነበረም ..በአተካሮ የተሞላ ውጥረት የነገሰበት አድርባዮች ፍራቻ ይነበብባቸው 
የነበረበት የነባር ታጋዮች ጩሐት ውይይቱት ደበላልቆት ያደረበት  እንደነበርበስብሰባው ላይ የነበሩ ተናግረዋል::
የት ከርሞ ከየት እንደመጣ ወዴትስ ሄዶ እንደነበር በማይታወቀው የአምባገነን ቡድን አስተባባሪ በደብረ ጽዮን
 የተመራው ይህአተካራዊ ስብሰባ የወያኔ አባላቱን ለከፍተኛ ፍጥጫ ከመዳረጉም አርፎ ዘለፋ እና ዛቻ
 እንዲሁም የቀድሞ ጉዳዮች ወቀሳ ያካተተ የነበረ ሲሆን በብኣዴን ነባር አባላት እና በጫካው ሕወሓት
እንዲሁም በሕወሃት የከተማ ህዋስ እና በጫካው ሕወሓት  መካከልከፍተኛ የሆነ ጭቅጭቅተስተናግዷል::
ዋናው አትኩሮት የነበረው ይላሉ ምንጮች ወቅታዊው የአንድነት ፓርቲእንቅስቃሴ;የሙስሊሙ ጥያቄ;
የምእራባውያን ጫና;እና የዲያስፖራው ድጋፍ በተመለከተ ነበር::
የስብሰባው ላይ አነጋጋሪ የነበረው የአንድነት ፓርቲ ጉዳይ በስፋት መንቀሳቀስ በዚሁ ከቀጠለ
ካለው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ችግር አኳያ ህዝቡ ሆ! ብሎ ሊነሳ ስለሚችል ከዚህ ቀደም እንደተለመደው
 ፓርቲውን በወከባእና በጥቅም ማክሰም ወይንም ከፓርቲው ጋር መደራደር እስከሚሉ ጨከን ያሉ ሃሳቦች
ተንጸባርቀዋል:: ከፓርቲዎች ጋር መደራደር የሚባል ነገር አይዋጥልኝም  የሚሉት አለቃ ጸጋዬ በቁጣ እና
በጩኽት ይህንን  የመደራደር ሃሳብ ያቀረበችውን የሕወሓት የከተማ ህዋስ አባልን ያመጣንሽ እኮ እንድትጦሪን
 እንጂ ጠላት እንድትሆኚን አይደለም በማለት በቋንቋቸው አይሆኑዘለፋ ዘልፈዋታል::
ቤቱ በዝምታ ድባብ እንዲዋጥ ያደረጉት የጫካው ሕወሓቶች የታገልነው ለድርድር አይደለም ሲሉ ተደምጠዋል::
ሰማያዊ ፓርቲ ቢነሳም ብዙም አያሰጋንም በሚል ታልፏል::
ከኦህዴድ ሙክታር ብቻ የተካፈለበት ይህ ስብሰባ 16 የህወሃት ጄኔራሎች የተመከሩ ይመስል
ጂንስ በጃኬት ለብሰው ነበር በስብሰባው ላይ የተገኙት :: በአሁን ሰአት የደህንነቱ እና የወታደሩ ክፍል በተጠንቀቅ
ሊሆን ይገባዋል በሚል የሚያሳዝን አንደበት መናገር የጀመሩት አቶ በረከት አትኩረውት የነበረው በሙስሊሙ እና
በዲያስፖራው ጉዳይ ነበር :: ሙስሊሙች ጥያቄያቸው ሰፍቶ አለምም ጆሮ ሰቷቸዋል እንሱን ዝም ማሰኘት
 አሊያም ለፖለቲካ ስልትመጠቀም አስፈላጊ ነው ቢሉም የታሰሩትን መፍታት ለኢህኣዴግ የፖለቲካ ኪሳራ ስለሆነ ያለንን
ሃይል መጠቀም አለብንብለዋል:የዲያስፖራው ጥላቻ ከ60% ወደ 90% አድጓል::
10% ደሞ ንብረት አገር ቤት ያፈሩ ወይም ከፖለቲካ ነጻ ነንየሚሉ ግለሰቦች ሲሆኑ ይህ ደሞ 10% ደጋፊ ሳይሆን
የምንላቸው ለንብረቶቻቸው እና ለቤተሰቦቻቸው ደህንነትየሚለማመጡ ብንል ይቀላል :: በዲያስፖራው ዘንድ
ያለው ጉዳይ ብዙም ተስፋ ሰጪ ስላልሆነ ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል::
ይህ የራሳችን የፖሊሲ ውጤት ነው ብለው ደፍረው የሚናገሩ አባላት አልተገኙም::
የህወሃት አንጋፋ ታጋዮች የተሳተፉበት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ያልተጠሩበት ጥቂት ብኣዴኖች እና አንድ ኦህዴድ
የፈጠጡበት ይህ ስብሰባ የምእራቡን
ጫና በተመለከተ ሰፋ ያለ የዲፕሎማቲክ ስራ እና ዝርዝር ሪፖርት ይዞ የማስረዳት ስራ እንዲሰራየሕወሓት የውጪ ጉዳይ
አትኩሮት እንዲሰጥበት ያደረገ ሲሆን ለአንድ አገር የውጪ ፖሊሲ የአንድ ፓርቲ ሰዎችን እንዲሰሩ ማዘዝ በአንዳንድ 
ተሰብሳቢዎች ላይ አግራሞትን ፈጥሯል:: ምንምአይነት ስምምነት ያልታየበት ይህ ስብሰባ በፍጥጫ በአተካሮ እና በጩኽት
የተሞላ ቢሆንም አብዛኛዎቹ አንጋፋ ታጋዮችማስታውሻቸው ላይ ሲቸከችኩ ተስተውለዋል:: ወደማይፈታ ችግር ራሱን
እየወሰደ ያለው ቡድናዊው አምባገነን ከፍተኛአጣብቂኝ ውስጥ እንዳለ የሚያሳየው ይህ ጨለማ የሚደረግ ስብሰባ አሁንም
እንደቀጠለ ሲሆን ሰዎች
እየተመረጡ ደጋፊዎችእየታዩ እየተጠራሩ በጎጥ እና በመንደር በመሰባሰብ ሃገርን ወደማትወጣበት አዘቅት ቁልቁል እየከተቷት ነው::
በመጪውቀናቶች የሚጠሩ ስብሰባዎች በእነዚሁ ወቅታዊ ጉዳዮን ላይ አተኩርው እንደሚወያዩ ይጠበቃል

No comments:

Post a Comment