Friday, March 21, 2014

ለአልሙዲ “ማፅናኛ”(ከጋዜጠኛ ተስፋዬ ተሰማ)

March 20/2014

በቅርቡ ባህርዳር ላይ በተካሄደው የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ሼኽ አልሙዲ በክብር እንግድነት ተጋብዘው ነበር። የበአሉን መክፈቻ በቲቪ ስከታተል አንድ ጥያቄ ወደ በአእምሮዬ መጣ። አልሙዲንን የክብር እንግዳ አድርጐ መጋበዙ ለምን አስፈለገ?..ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። “የገዢው ፓርቲና የባለስልጣናቱ ታማኝ ወዳጅ ስለሆኑ፣ በባህርዳሩ ስታዲየም ግንባታ ድርጅታቸው ስለተሳተፈ ወይም ሼኹ ለስፖርት ያላቸውን ፍቅር በማየት..” የሚሉ ነገሮችን መደርደር ይቻላል።

በእኔ ግምት አልሙዲ በባህርዳሩ በአል በእንግድነት የተጋበዙት በሰሜን አሜሪካ ስፖርት በአል ላይ ስለተዋረዱ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት የፈጠርዋት ማፅናኛ ትመስለኛለች። ባለፈው አመት እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ሳምንት ሁለት የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ተከበሮዋል። አንድኛው በሼኽ አልሙዲና የዳይስፖራውን ማንነትና ፍላጐት ባልተገነዘቡ ወዳጆቻቸው የተዘጋጀ ነበር። በነዚህ ወገኖች ግምት “ዳያስፖራው በተወሰኑ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ካድሬዎች የሚሽከረከር የዋህ ህዝብ” አድርገው ይወስዱታል።

 አሜሪካ ሀገር ከኅይለስላሴ ጀምሮ በደርግ ጊዜ ከዛም በኋላ የመጣው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ (በምንም መንገድ አሜሪካ ይምጣ) ለዘሩ፣ ለጐሳው ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነቱ ጥልቅ የሆነ ፍቅርና ክብር አለው። በዚህ ምክንያት የኢህአዴግን የዘር ፖለቲካ አይደግፍም። ከደጋፊዎቹም ጋር የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ የገባው በዚህ አገር ወዳድ አቋሙ ነው። ይህ እውነት ያለገባቸው አልሙዲና ተከታዮቻቸው በስፖርቱ አስታከው ዳያስፖራውን እንቆጣጠራለን በማለት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢከሰክሱም አልተሳካላቸውም። ባዶ ስታዲየም ታቅፈው ነው የቀሩት። ሁለተኛው ኢ.ኤስ.ኤፍ.ኤን የሚባለው ኢትዮጵያዊ ፌዴሬሽን የነሱን ያክል ገንዘብ ሳይኖረው በርካታ ህዝብ ከጎኖ ማሰለፍ ችሎዋል። እንዲያውም ስታዲየሙ ሞልቶ ሰው እስኪመለስ ድረስ። በዚህ በአል ከፍተኛ የሆነ የአንድነትና የአገር ፍቅር ስሜት የታየበት፣ የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ ብሎ በብዛት የተውለበለበበትና ያሸበረቀበት፣ ሰዎች ከብሄራቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነታቸውን ያገነኑበት ትልቅ በአል ነበር።

ባዶ ስታድየም የታቀፉትና አፍረው በውርደት ለተመለሱት አልሙዲ የባህርዳሩ እድል በማፅናኛነት ተሰጣቸው። ኢትዮጵያዊያን በነፃነት በሚኖሩበት አሜሪካ ግን አልሙዲ በገንዘባቸው የህዝብን ድጋፍ መግዛት አይችሉም። በገንዘብ ምንም ማድረግ እንደማይችሉም ሊያውቁት ይገባል።

ሴቶች ለዓገራቸው ነጻነት የሚያደርጉትን ተሳተፎ በመደገፍ ኢትዮጵያ ዓገራችንን ካለችበት ስቃይ እንታደጋት....!!!

ራሄል ኤፍሬም
ቀደም ካለው ከሴቶች ተሳትፎ በመነሳት አውን እስካለንበት ጊዜ እንስቶች በፖለቲካው ያላቸውን ትልቅ ሚና ላነሳ ወዳለው።
በሁሉም የማህበራዊ ህይወት ዘርፎች ውስጥ የኢትዮጵያ ሴቶች የሚጫወቱት ጉልህ እና ወሳኝ ሚና ያላቸው ቢሆንም ሃገሪቱ ባላት ባህል፣ ታሪክ፣ እና ፖለቲካዊ ስርአት ምክንያት በሁለንተናዊ ማህበረሰብ እድገት ያደረጉት አስተዋጽኦ ተገቢውን ትኩረትና እውቅና አላገኘም። በዚህ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አግላይ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እና ማህበረሰባዊ ህግና ደንቦች ምክንያት ሴቶች የልፋታቸውን ውጤት ሳያገኙ ቆይተዋል። እንደሚታወቀው ሴቶች የዓለማችን ግማሽ አካል እንደመሆናቸው መጠን ተገቢውን ስፍራ ሳይሰጣቸው ነገር ግን በዘልማድ በማህበርሰቡ ውስጥ ሴቶች በዓገር፣ በእናት፣በሚስት ይመሰላሉ። እንዲሁም አንዳንድ ጊዜ ከታዋቂ ወንድ በስተጀርባ ጠንካራ ሴት እንዳለች ቢነገርም በማህበረሰብ ውስጥ ያላቸውን ተገቢ ቦታ እና እውቅና አልተስጣቸውም። ቀደም ባሉ ጊዜያት ሴትልጅ ከቤት ስትወጣ ነውር በሆነበት ወቅት አጠቃላይ የቤት ውስጥ ስራ ሃላፊነት በተለይም ለወንዶች ምግብ አዘጋጅቶ የመጠበቅ ግዴታ የሷ ሲሆን፣ከማጀት ስራዋ በተጓዳኝ ዓገር ተረካቢ ዜጋን የማምረት እና የማሳደግ ጫናው የዚችው የምስኪኗ ሴት ሓላፊነት ነበር ።

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ብዙ ታሪክ የሰሩ ጀግኖች እናቶች ቢኖሩም ባለው ማህበረሰባዊ አፈና ምክንያት በሴቶች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ጉልህ ሚና ሳይጫወት ቀርተዋል። እነዚ ቆራጥ እና ጀግና ታሪካዊ ሴቶች በወቅቱ የነበረውን ዋላቀር  አስተሳሰብ በመቋቋም በድፍረት እና በጀግንነት ከወንዶች በስተጀርባ በመሆን ላገራቸው ነጻነት ያላቸውን ተሳትፎ በቆራጥነት አሳይተዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜም የሴቶች እንቅስቃሴ እየተሻሻለ የመጣበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የግል ጥቅሙን በማራመድ ላይ በሚገኘው በዚህ አረመኔ መንግስት ምክንያት ዓገራቸውን ትተው በስደት ላይ የሚገኙ እና የትውልድ ዓገራቸው ላይ እንደ ሁለተኛ ዜጋ  በመቆጠር በስቃይ ላይ የሚገኙ  ቆራጥ ሴት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓረቲ አመራሮች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። ይህም የሆነበት ምክንያት በአገራቸው የፖሊቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበረስባዊ ሁኔታ በጉልህ መብቶቻቸውን ለመተግበር እና ስለ መብቶቻቸው ተሟጋች እንዲሆኑ ስለማይፈቅድ ከውጭ በመሆን ባገራቸው ለውጥ ለማምጣት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። ዛሬ በግለሰብም ሆነ በድርጅት ደረጃ  የሴቶች ተሳትፎ እድገት እንዲጨምር ትልቁን የህይወት መሰዋትነትን ከፍለው ያለፉ እንዲሁም እየከፈሉም ያሉ ጀግና እንስቶች ለኛም ሆነ ለዓለም ትልቅ ምሳሌወቻችን ናቸው ።

በኢትዬጽያ ውስጥ የፖለቲካና ሲቪክ መብቶች ከሆኑት ውስጥ የመናገር፣ የመጻፍ፣ እና በአጠቃላይ ሃሳብን በነጻነት የመግለጸ መብት በሌለበትና በተገደበበት ሁኔታ ገዢው መንግስት መስማት የሚፈልገውን ብቻ መናገር እና መጻፍ ግዴታ በሆነበት ቦታ ላይ መስዋእትነት የሚከፍሉ ሴቶች ቁጥር ከፍተኛ ነው። ለዓገራቸው፣ ለወገኖቻቸው እና ለነጻነታቸው በመቆም አምባገነናዊ ስርአትን በመታገል የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ። ለህዝብ ደህንነትና መብት ደንታቢስ የሆነው  በስልጣን ላይ የሚገኘው  ይህ ክፉ መንግስት ሴቶች እህቶቻችን እና ወገኖቻችን በነጻነት በመናገራችው፣በመጻፋቸው ፣በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመቃወማቸው እና የሚፈልጉትን ፓርቲ በመምረጣችው ብቻ አሸባሪ በማለት እስር ቤት በማጎር ይገኛል።
 ከነዚህ ጉልህ ሚና ከሚጨወቱ ሴቶች እህቶቻችን መካከል በሰብአዊ መብት ተሟጋችነት እና በጋዜጠኝነት እንዲሁም በግለሰብም ሆነ በድርጅት ደረጃ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙትን እንስቶች እንዳሉ እና ከነዚህም መካከል እንደ ነብርቱካን ሜዴቅሳ እና እንደ  ሪዖት አለሙ ወ.ዘ.ተ ያሉ ለኛ ትልቅ ምሳሌ የሚሆኑን ጀግና ሴቶች ናቸው ።

የጀግኖቻችንን ምሳሌ በመከተል የአለም አቀፍ ሴቶች ቀን ማርች  8  በተከበረ ማግስት በአዲስ አበባ በተደረገ የሩጫ ውድ ድር  ከተሳተፉ ሴቶች መካከል አጋጣሚውን በመጠቀም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ እና በማህበራዊ ኑሮ የ ሚደርስባቸውን አፈና እና ጭቆና በማሰማት መብታቸውን ለማስከበር ጠንካራ ቋም እንዳላቸው ያሳዩበት አጋጣሚ ነበር። ይህም ክስተት ሴቶች እህቶቻችን ልክ እንደ ቀድሞው አሁንም የወገኖቻችንን ድምጽ ማፈን እና ማሰቃየት የለት ልማዱ ያደረገውን የወያኔ መንግስት የሚያደርስባቸውን ከባድ ጫና ወደጎን በማድረድ ድምጻቸውን ከማሰማት እና ችግሮቻቸውን ከማሳወቅ ወደዋላ ሳይሉ  ከፊታቸው የተደቀነ መሳሪያና የሚደርስባቸውን እስር ሳያስፈራቸው አምባገነናዊ ስርዓቱ እያደረሰባቸው ያለውን ጭቆና በተቃውሞ ገልጸዋል።

ሴቶች ለዓገረቸው በፖለቲካው ዘርፍ ከፍተኛ ሚና በሚጫወቱበት በዚህ ወቅት አበረታች እና ተስፋ የሚጣልባቸው አዲስ ጀግና እና ለመብታቸው ተሟጋች ትውልዶች እየመጡ እንዳሉ በተግባር እያየን ነው።  ከጎናቸው በመቆም የህቶቻችን ድምጽ እንዲሰማ አስተዋጽዖ በማድረግ ያሉበትን ስቃይ እና መከራ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በማሰማት በወያኔ መንግስት ላይ ውግዘትና ውርደት ማድረስ ተገቢ ነው። ዓገራችን ካለችበት ከባድ ችግር ለማውጣት አንዱ እና ዋንኛው የሴቶች ተሳትፎ እንደመሆኑ መጠን ያላቸውን የመስራት ትልቅ ችሎታ ግምት ውስጥ በማስገባት ለዓገራቸው ነጻነት የሚያደርጉትን ተሳተፎ በመደገፍ ዓገራችን ካለችበት ስቃይ እንታደጋት።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ..!!

Friday, February 7, 2014

ወደ አዋጅነት ይቀየራል የተባለው ‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባና የዕድሳት አገልግሎት›› ረቂቅ መመርያ ኃላፊነት የጎደለው እንዳይሆን የብዙዎች ስጋት ነው።

ሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን 

 የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከ‹‹ኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› ጽ/ቤት ጋራ በመተባበር ያዘጋጀውና ከጥር 30 – የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም. በሐዋሳ – ሌዊ ሪዞርት ‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባና የዕድሳት አገልግሎት›› ረቂቅ ላይ ለውይይት እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል። ይህ ከመመሪያ ወደ ዐዋጅነት ይቀየራል እየተባለ የሚነገርለት መመርያ ምንነት እስካሁን በዝርዝር አልታወቀም።

‹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዋጁ ረቂቅ እንዲሰጣት እና አስተያየትና አቋም ለመውሰድ ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ያቀረበችው ጥያቄ ምላሽ  አለማግኘቱን ሐራ ተዋሕዶ የተሰኘው ብሎግ ጥር 28/2006 ዓም ገልጧል።

በኢትዮጵያ ከ 1952 ዓም ወዲህ ምንም አይነት ሃይማኖትን የተመለከተ አዋጅ  ወጥቶ አያውቅም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከ 40 ሚልዮን በላይ ተከታዮች ያሏት እና ክርስትና ከተመሰረተ ጀምሮ ላለፉት ከ 2000 አመታት በላይ ለሆኑ ዘመናት  በኢትዮጵያ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት የፍቃድ እና የምዝገባ መስፈርት ተጠይቃ እንደማታውቅ ይታወቃል።ደርግም በዘመኑ ምንም አይነት ሃይማኖታዊ አዋጅ አለማውጣቱ ይታወሳል።ይህ ወደ አዋጅ ያድጋል የተባለው መመርያ ኃላፊነት የጎደለው እንዳይሆን የብዙዎች ስጋት ነው።

ጉዳያችን
ጥር 30/2006 ዓም 

ሰበር ዜና በሪያድ የኢትዮጵ ኮሚኒቲ ማህበር ስራ አመራ ማምሻውን ጠርቶት የነበረው ስብሰባ ሳይጀመር በሁከት ተበተነ !

Ethiopian Hagere's photo.Ethiopian Hagere's photo.

በሳውዲ አረቢያ የሪያድ ኮሚኒቲ ማህበር ስራ እመራር ኮሚቴ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በታደሙ አባልት እና የአንባሳደር ዶ/ር መሃመድ ሃሰን የቅርብ ዘመድ እንደሆኑ በሚታወቁት የቀድሞው የኮሚኒቲ ሊቀመንበር ሼክ ሙስጠፋ ሁሴን አሊዬ ደጋፊዎች መሃከል ተነስቶ የነበረው አለመግባባት ወደ ግጨት አምርቶ እንደነበር ምንጮች ከሪያድ ገልጸዋል። 

የስብሰባውን ታዳሚ ግራ ያጋባው ይህ ግጨት መነሻው የቀድሞው የማህበሩ ሊቀመንበር እንደነበሩ የሚነገርላቸው ሼክ ሙሰጠፋ ሁሴን ለምን ከስልጣኔ ተነሳሁ በሚል በምከትል ሊቀመንበሩ አቶ ቃሲም ላይ ቡጢ መሰንዘራቸውን ተከትሎ መሆኑንን የሚናገሩ ወገኖች ሼክ ሙስጠፋ ከስብሰባው በፊት ሲያስተባብሯቸው የነበሩ ከ 50 የሚበልጡ ደጋፊዎቻቸው ባስነሱት ሁከት የመስብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ፡ ከፍተኛ ውጥረት ነግሶ ማምሸቱን ጠቅሰዋል። ....
ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ግዜ በአካቢው የተፈጠረውን አለመረጋጋት የማህበሩ ስራ አመራር ኮሚቴ ስብሰባውን ለሌላ ቀን ለማስተላለፍ መገደዱን የሚገልጹት ምንጮች የሼክ ሙስጠፋ ደጋፊዎች ጩቤ ታጠቀው ወደ አዳራሹ ገብተው እንደነበር ቢገልጹም በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳርሽ ውስጥ ዛሬ በተነሳው አንባጓሮ የተጓዳ ሰው እደሌለ አረጋግጠዋል ። ሼክ ሙስጠፋ ሁሴን ቀደም ሲል በሪያ የኢትዮጵያ ኮሚቲ ለቀመንበር እንደንበሩ እና ምንጩ በግልጽ የማይታወቅ ሁለት ሚልዮን ሪያል በግል ካዝናቸው ተገኝቶ በሳውዲ መንግስት የደህነንት ሃይሎች ታስረው መክረማቸውን ተከትሎ የማህበሩ ስራ አመራር ኮሚቴ በማህበሩ መተዳደሪያ ህገ ደንብ መስረት የስልጣን ሽግሸግ ለማድረግ በመገደዱ ግለስቡን ከሃላፊነታቸው ማስወገዱን ይናገራል። ዛሬ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳርሽ ተከስተ በተባለው ሁከት በሳውዲ የኢትዮጵያው አንባሳደር ዶ/ር መሃመድ ሃሰን እጅ እንዳለበት የሚገልጹ ወገኖች ሃገር እና ህዝብን ወክሎ ከተቀመጠ አንባሳደር የሚጠበቅ እንዳልሆነ በማውሳት ድርጊቱን አውግዘዋል።

ሼክ ሙስጠፋ ሁሴን አሊዬ የአንባሳደር ዶ/ር መሃመድ ሃሰን ዝምድናን መከታ በማድረግ በኤንባሲው ማህተም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ከሚገኙ የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ በጎ አድራጊ ድርጀቶች ገንዘብ በመሰብሰብ ከአንባሳደሩ ጋር ለግልጥቅማቸው ሲያውሉ የነበሩ መሆናቸውን የሚያወጉ የሪያድ ነዋሪዎች ሼክ ሙስጠፋ ሁሴን ኢትዮጵያ ውስጥ በከፈቷቸው 2 ኤጀንሲዎቻቸው በመታገዝ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እስከ 7 መቶ ዶላር በመሰብሰብ በእህቶቻችን ህይወት ሲነግዱ የነበሩ ከመሆናቸውም በላይ በህገወጥ የሃላ ንግድ ተሰማርተው ከቀርብ ግዜ ወዲህ የከበሩ ሃብታም ነጋዴ እና የአንባሳደር ዶ/ር መሃመድ ሃሰን ባለው ለታ መሆናቸው ይናገራል ።

ዛሬ ተቀሰቀሰ በተባለው ግጨት ዙሪያ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ የዲያስፖራውን ሃልፊ ለማንገጋር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም ።
በአቶ ሙስጠፋ ሁሴን ከወኒ መወጣት እና እጃቸው ላይ ተይዞ ስለነበረው 2 ሚልዮን ሪያል « 10 ሚልዮን ብር » የድረሱንን መረጃዎች ወድፊት አጠናቅረን ለህዝብ ይፋ እንደምናደርግ ከወዲሁ እንገልጻለን፡፤

Sunday, October 27, 2013

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ ኤርትራ በተገነጠለችበት ወቅት መሆን ያለበት ይህ ነበር።

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ፡ በሊግ ኦፍ ኔሽን የሚታወቀውና፡ እንደአውሮፓ አቆጣጠር በ1961 የተባበሩት መንግሥታት ካጸደቃቸው ሦሥቱ የኤርትራ ሁኔታ ውሳኔ፡ ” ኤርትራ የፊዴሬሽኑን ሁኔታ ሕዝቡ ካልፈለገና ካርታዋ ከተገነጠለች፡ ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽን ወደሚታወቀው እዚህ ላይ ወደሚታየው ካርታዋ ይመለሳል ነበር። 
የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሽስት ወያኔ ሞተር መለስ ዘባንዳዊ፡ ወደብ ሸቀጥ ነው በሚል የብልግናና የውንብድና ንግግሩ፡ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉትን የግብር ገንዘብ ለጂቡቲ በቀን ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገብር ታውቃላችሁን? 
በውጭ ሃገር የሚገኘው ታላቁ የኢንተርኔት ሚዲያ ” ኢትዮሚዲያ ” በፊተኛው ገጹ ላይ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” በማለት ለተወናበደው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ ነው።በትክክለኛው በነአጼ ምኒልክም ይሁን በሊግ ኦፍ ኔሽን እንዲሁም የኤርትራ ፌዴሬሽን በጸደቀ ወቅት መገንጠልን ሕዝቡ የሚፈልግ ከሆነ፡ በተባበሩት መንግሥታት የሚታወቀው ይኸው ካርታ ነው። ወያኔዎች ስለድንበርም ይሁን ስለባሕር በር የመሃይማን፤ የጫካ አፈራሽ ዱርዬዎች ናቸው።
መለስ ዘባንዳዊ ወደብ ሸቀጥ ነው ብሎ ለጂቡቲ በቀን 6 ሚሊዮን ብር የኢትዮጵያ ሕዝብ የግብር ገንዘብ እንዲጠፋ ያደረገውና ኢትዮጵያን ጭለማ ያደረገው።
ታላቁ የኢትዮጵይውያን የውጭ ኢንተርኔት “፡ኢትዮሚዲያ የፊት ገጽ ላይ የተጻፈው፦ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” እውነት ነው። በወያኔ ኢትቪና ሌላችም ፕሮፓጋናዳዎች የተወናበደው በተለይም የመከላከያ ሠራዊት ነኝ ለኢትዮጵያ ቆሜያለሁ የሚል ካለ እውነታው ይኸው ነው።
Fresenay Kebede

Residents in Gambella set Indian-owned farm on fire

420013_215543375240044_2099309808_n
oct27,2013
Residents of the Gambella Regional State, Godera woreda, attacked and set the property of the Indian farm, Verdanta Harvest Plc., on fire on account of destroying the rich forest resources in the woreda where Verdanta has some 5,000 hectares for tea plantation.
According to sources in the area, the vigilantes attacked the plantation compound on Tuesday late night and set ablaze stores, fuel tankers, machineries like tractors and excavators and logs of timber, allegedly harvested from the land the company took for tea plantation. Gatlowak Tute, president of the region, confirmed the occurrence and said that a 9-man team has been sent to the area to investigate the event. “So far, security forces have taken into custody few locals suspected of involvement in the incident,” Gatlowak told The Reporter.
Verdanta took over the plantation five years ago from the Ministry of Agriculture on a 50-year lease contract with fairly cheap terms. According to the contract signed at the time, the company agreed to pay 111 birr annual lease price for the plantation extending 3012 hectares wide in Godera woreda and Gumare kebele. The total lease quotation of 16.7 million birr was agreed to be payed over the course of the 50 years at 334,332 birr per annum.
However, Verdanta requested the land for tea plantation before the ministry took over the land provision from the region and hence was able to receive 5,000 hectares although the contract with ministry say 3012. According to sources, the company have kept control of the 5,000 hectares until present, which residents of the area consider to be a forest resource and national forest region. The two kebeles of Godera woreda, Gomare and Kubu, are among the 58 primary national forest regions in the country. According to residents in the locality, the area is also rich in forest agricultural productions like honey, spice and coffee.
The vigilant residents say that the plantation company was offered is indeed a forest area that deserves to be preserved. Whereas both the regional government and the ministry say that the plot of land is no more than scattered bushes and that it does not qualify to be called a forest. According to the Food and Agricultural Organization (FAO) standards, a forest area can be referred to as such as long as it is at least half a hectare wide and have trees more than five meters tall. Residents say that even the plot that is held by the Verdanta is 5,000 hectares and that it has tree which are 10 meters tall in length. At one time former president of the republic, Girma Woldegiorgis appealed to both the ministry and the region not give the land which should be preserved as national forest area. Tea plantation require the entire vegetation to be cleared out from the area, hence the president appealed to reconsider the decision. However, both the ministry and regional administration did not want to accept the request and hence the company stayed in possession of the property until the incident.
On the other had, the widespread rumors accusing the Verdanta of harvesting timber from the forest while it was supposed to be planting tea was also not accepted by the authorities. Sources say that on quite various occasions authorities have discovered logs of timber products leaving the property of Verdanta. However, the regional president did not deny this but said that the company have has assured his administration that the timber is not for sale. Although not verified by the findings of the investigating committee yet, sources indicate that it was the vigilantes of Godera who have taken matters into their own hands.
Development Bank of Ethiopia (DBE) have provided 89.5 million birr in loans to Verdanta. Hence, some are asking if DBE collateral has been damaged in the process. Efforts to get response from the Bank was not fruitful, and other are also asking if the investigative committee could come up with an amicable solution for the residents and the company in question.

የትርፍ ሰዓት ትግል


ኢዮብ ይስኃቅ
ከዕለታት አንድ ቀን ባልተለመደ ድፍረት የሙስና ኮሚሽን ሰይፉን ትላልቅ የወያኔ ባለሥልጣናት ላይ አሳረፈ። እንደመድኃኒት ብልቃጥ እዚህም እዚያም ተወሽቆ የነበረ ብርና ንብረት እያስቆጠረ ወንጀለኞቹን ዋስ እየከለከለ ወደ ወህኒ ወረወረ። ሚኒስትሮች ከቦታቸው ተፈናቀሉ፤ የሙስና እናት የሚለውን ሜዳሊያ ያጠለቀችው ወ/ሮ አዜብ ከኤፈርት ተባረረች። ያዲሳባ ከንቲባነትም ሱሚ ነው ተባለች። ከሁለት ብቻ ሳይሆን ከብዙ ያጣች ሆነች። ህዝቡ እልል ለማለት ቢፈልግም ወያኔን ስላላመነ መጨረሻውን ለማየት መጠባበቅ ያዘ።
 የተፈራው አልቀረም ጉዱ ቀስ በቀስ ይወጣ ጀመር። በትሩ አንደኛው ጠንካራ ሙሰኛ ሌላኛውን ደካማ ሙሰኛ የሚያስገብርበት ሂደት ነበር። ህወሓትን ሊጋፋ ይችላል ተብሎ የተጠበቀው በረከት ስምኦን ጉዋደኞቹን ካስበላ በኋላ ተደራድሮ ለሌላ ሥልጣን ታጨ። ምናልባት ትግርኛ መናገሩ ከአደገኛው ሰይፍ ሳይታደገው አልቀረም – ለዛሬ።
ሰሞኑን የተስፋዬ ገብረአብ እና የተመስገን ደሳለኝ ከቅርብ ምንጮች ተገኘ ተብሎ የተጻፈውን የኢህአዴግን መበላላት የሚያሳይ ጽሑፍ ሳነብ፤ በተጨማሪ የተገነዘብኩት ነገር እስሩና መጠላለፉ ለሀገሪቱ ጥቅም ሳይሆን የወያኔን የሥልጣን ግዜ ማራዘሚያ መሆኑን ነበር። በተለይ ተመስገን አቶ ስብሃት ነጋ “በውራይና” ጋዜጣ ላይ የፃፉትን ሲያስነብበን የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር በፍፁም ሥልጣኑን የማስረከብና ለኢትዮጵያም ምንም አይነት የሚጠቅም ራዕይ እንደሌለው ያረጋገጠ ነበር። ምናልባት ራዕይ እንኳን ቢኖራቸው፤ በሥልጣን ላይ እስከነድዳቸው የመቆየት ሊሆን ይችላል። መቆየታቸው ባልከፋ! ነገር ግን ለዚች ድሃ ሀገርና ህዝብ የሚጠቅም አንድም ፖሊሲ የመቅረፅ ሃሳብ የላቸውም። እያንዳንዱ ልማት ተብዬ ከጀርባ ለነሱ ሙስና የተጋለጠ ካልሆነ በስተቀር ለሀገር ተብሎ የሚወጣ ዕቅድ የለም። ለሰው ልጅ ምን ያህል ሀብት ይበቃዋል ብለን እስክንገረም ድረስ በአጥንቱ የቀረውን ህዝብ እየጋጡት ይገኛሉ።
የመገናኛ ብዙኀኖቻችን
ባለፉት ሃያ ዓመታት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ስንመለከት በአዲስ ዘመንና አጋር የመንግሥት ሚዲያዎች እንደሚነገረን የጥጋብ ሀገር አልሆነችም። ወይንም በዘመናዊው አዲስ ዘመን “ሪፖርተር” ጋዜጣም እንደሚቀርብልን የኢትዮጵያ ችግር የጠንካራ ተቃዋሚ መጥፋት ብቻ አይደለም። ስታትስቲክ ብቻውን ዜና አይደለም ብሎ በአሉ ግርማ እንዳለን፤ የተመደበውን በጀት ድምር፣ የሚሠሩ ልማቶች ወጪና የተገኘውን ብድር በደማቅ ርዕሶች መፃፍ ብቻውን ጥሩ ጋዜጣ አያሰኝም። በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ድህነት፣ በየትምህርት ቤቱ ለሁለትና ለሦስት ቀናት እህል ባፋቸው ሳያልፍ በየክፍላቸው የሚወድቁትን ህፃናትና በየቀኑ በልማት ስም የሚፈናቀሉትን ቤተሰቦች ዜና እንደግል ጋዜጣነቱ ሲያስነብበን አናይም። አልፎ አልፎ ተኝቶ ቤቱ ድረስ የሚቀርቡለትን ትኩስ መረጃዎች ለማጀብ ቀላል ትችቶችን በርዕሰ አንቀፁ ያቀርብልናል።
እንደአለመታደል ሆኖ በሌሎችም የግል ጋዜጦች የምናገኘው ዜና ጽንፈኝነትን የተሸከመ ከመሆኑም ሌላ መንግሥትን ከመሳደብ ውጪ በተቃዋሚ ጎራ ያለውን ችግር ግልፅልፅ አድርገው አያቀርቡም። እየተሳደደም ቢሆን ሁሉንም በአንድ ሚዛን የሚያስቀምጠው አንድ ለናቱ የሆነው ተመስገን ደሳለኝ ብቻ ነው።
በሀገር ውስጥ ያለው ተቃዋሚ
በርግጥም ወደ ተቃዋሚ ጎራ ስንመጣ ቀላል የማይባል ችግር አለ። በመጀመሪያ ባገር ውስጥ ያሉትን ስንመለከት አብይ ችግር ሆኖ የምናገኘው ሥልጣንን ሙጭጭ የማለት ጉዳይ ነው። የሊቀመንበርነቱን ቦታ አስረከቡ ሲባል አረፍ ብለው ይመለሱበታል። በዚህ ሃያ ዓመት ውስጥ የትኛውም አንጋፋ ፓርቲ በአዲስ ወጣት መሪ ተተክቶ አላየንም። ተተካካን ያሉትም በአጋፋሪነት ከኋላ በምክትልነት ያስከተሉዋቸውን ሰዎች ነው። እነዚህ ሰዎች እንደአስፈላጊነቱ ቦታውን ሊለቁ የሚችሉ ታማኝ ሰዎች ናቸው። በተቃዋሚነት ዘመኑ ዲሞክራሲን ያላለማመደን መሪ በአጋጣሚ የመንግሥት ሥልጣን ቢረከብ እንዴት አይነት አምባገነን እንደሚሆን ለመገመት ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም። ለጠንቋዩ የታሰበውን እራሳችን እየበላን እራሳችን እንገምታለን።
 ስደተኛው ተቃዋሚ
ወደውጪው ተቃዋሚ ስንመጣ ሰሞኑን “ሰላቢ ፀሐፊዎች” በሚል በተስፋዬ ገብረአብ የቀረበውን ጽሑፍ በማስታወስ ነው። ተስፋዬ ይህን ያለው በብዕር ስም ጎርፍ የሚለቁትን ፀሐፊዎች ለመንካት ነው። እኛ ደግሞ ሰላቢ ፖለቲከኞች እንላለን – ቁርጠኝነት ጎሎዋቸው የሌላውን የትግል ስሜት ይሰልባሉና። በትክክል የምንስማማበት አንድ ነጥብ አለ። ይኸውም ኢትዮጵያ ፋታ በማይሰጥ አጣብቂኝ ውስጥ እንዳለች። ይህ ማለት ማቄን ጨርቄን ሳንል የምናምንበትን ወይም የምንሰብከውን ትግል መከተል ይሆናል። ወድድንም ጠላንም የዛሬዎቹ መሪዎች በረሃ በገቡበት ወቅት ወጣትነታቸውን ጨምሮ ብዙ ጥቅሞቻቸውን መስዋዕት አድርገው ነው።
ለምሳሌ መለስን እና ኢሳያስ አፈወርቂን ብንወስድ፤ አንዳቸው የተከበረ ዶክተር፣ ሌላኛቸው ደግሞ ኢንጅነር የመሆን ተስፋ የነበራቸው ወጣቶች ነበሩ። በሀብትም ቢሆን ደጃዝማች አባቶቻቸው መሶባቸው ሙሉ፣ ጎተራቸው ካመት ዓመት የማይጎድል ባላባቶች ነበሩ። ጥሩ ኑሯቸውንና የነገ ትልቅ ሰው የመሆን ዕድላቸውን በሳጥን ቆልፈውበት ነው ወደ በረሃ የገቡት። አይ! አሸንፈው መሪ ለመሆን ነው የሚል የዋህ ያለ አይመስለኝም። ኃይለሥላሴም ሆኑ ደርግ ይወድቃሉ ብሎ እንኳን ሰዉ እግዜሩም እርግጠኛ የነበረ አይመስለኝም። የራሱን ጀግኖች እየበላ መንገዱን ጠርጎ ያስገባቸው ወደድንም ጠላንም ኮሌኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ነው።
ይህ እንዲህ ሆኖ ሳለ የዛሬዎቹ ተቃዋሚዎች በተለይ ደግሞ ብቸኛው አማራጭ የትጥቅ ትግል ነው የሚሉት፣ እንኳን ሕይወታቸውን፣ ደሞዛቸውን ሲሰዉ አናይም። ኢትዮጵያ ያለችበት ችግር አጣዳፊና ግዜ እንደማይሰጥ ከተስማማን ፈጣን እርምጃ መወሰድ ነበረበት። ከዚህ ይልቅ መግለጫዎችን በመስጠቱ ላይና ገቢ ማሰባሰቡ ላይ በርትተው ሲንቀሳቀሱ እያየን ነው።
ከጥቂት ዓመታት በፊት በድል ማግስት አዲስ አበባ የሚያስገባ ካርድ በገንዘብ የሚታደልበት ዝግጅት ተደርጎ ነበር – በግንቦት ሰባት። በዚህ አጭር ጊዜ ወያኔ ወድቆ አዲስ አበባ ይያዛል የሚል የየዋህ ግምት ባይኖረኝም በኢትዮጵያ ተራሮችና ጫካዎች ውስጥ እየተሽሎከለከ ወያኔን የሚያሸብር ታጋይ መጠበቄ አልቀረም። በኢንተርኔት መስኮቶች ወዛቸው ግጥም ያለ ባለስካርፍ ታጋዮችን ተመልክተናል። ግን የዋሉበትን የትግል አውድማ በስህተት እንኳን ሰምተን ወይንም አይተን አናውቅም።
አንድ እየተሠራ ያለ ነገር ቢኖር ይሔ እንደጉድ ድህነትንና ግፍን እየሸሸ በረሃና ባህር የሚበላው ወጣትና ወደ ዐረብ ሀገር የሚሰደዱ እህቶች ምርጫቸው ሽሽት ሳይሆን የችግሮቻቸው ምንጭ የሆነውን መንግሥት ለመጣል ትግሉን መቀላቀል ነበር። ይህ መሆኑ ቀርቶ ግን በኢትዮጵያ ጫካዎች ልናያቸው የሚገቡ ወታደራዊ ልብሶች እንደእንቁጣጣሽ ቀሚስ እነታማኝ በየነን በፈንድሻ ለመቀበል በየስደቱ መድረክ ላይ ሲጌጥባቸው እናያለን።
 ኢትዮጵያን ከህወሓት ጥፋት ለማዳን ያለን ምርጫ
ሀገራችን በህወሓት መራሹ መንግሥት እጅ ከቆየች ያለማጋነን በሚቀጥሉት ዓመታት ዛሬ ያለችበት ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንደማይኖራት ማወቅ አለብን። ህዝቡም በዘርና በኃይማኖት ተከፋፍሎ እርስ በእርሱ የሚበላላባት ምድር ትሆናለች። ስለዚህም የትርፍ ጊዜ (part time) ትግል ለዚች ሀገር እንደማይመጥን አውቀን የመረጥነውን የትግል መስመር በቁርጠኝነት መቀጠል አለብን። በሰላማዊ ከሆነ በሰላማዊ፣ በትጥቅ ትግል ከሆነ በቦታው እታች ወርዶ መታገል ያስፈልጋል። ይህ ካለሆነ ግን የቁርጠኛ ልጆችን መንገድ በመሪነት ስም በመዝጋት በእጅ አዙር የወያኔ መንግሥት ዕድሜ እንዲራዘም ማገዝ አይገባም።

ትንሽ መልዕክት ለተስፍሽ (ተስፋዬ) ገብረአብ
በመጨረሻ ከላይ ስሙን ለጠቀስኩት ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ የምለው አንድ ወንድማዊ ምክር አለ። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ አሁን በቅርብ ደግሞ ለላይፍ መጽሔት በሰጠው ቃለመጠይቅ ስለኤርትራ ለምን እንደማይፅፍ ተጠይቆ “ሰዎች የማላውቀውን እንድጽፍ ለምን ይጠብቃሉ” የሚል መልስ ሰጥቷል። ወይንም በሚቀጥለው መጽሐፉ በአንዲት ምዕራፍ እንደሚያወጋን ተናግሯል። እኔ ግን የቡርቃ ዝምታን የሚያክል መጽሐፍ ለመጻፍ አርባጉጉ ወይ በደኖ ካሳለፈው ጊዜ የበለጠ በኤርትራ ቆይቶዋል የሚል ግምት አለኝ። በእናቱ ኤርትራዊ ቤተሰብ ውስጥ ማደጉ የኤርትራዊያንን ሕይወትና ኑሮ ከሌላው ሰው በተሻለ የማወቅ ዕድሉ አለው። ለአንድ አይደለም ለዕድሜ ልኩ የሚበቃ መጽሐፍ የሚወጣው ግፍ በኤርትራ ምድር እየተፈጸመ ነው። ተስፍሽ ደራሲ ድንበር እንደማይወስነው ላንተ መንገር የለብኝ። ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለህ ማመንህም ቢሆን ስለጎረቤት ሀገር ህዝብ መበደል ስለመጻፍ ሊገታህ አይገባም። ብዕርህ ስለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ስለመላው አፍሪካ ህዝብ መዘመር ይገባታል።
ይህቺን ትንሽ ጽሑፍ ከጫርኩ በኋላ በኢንተርኔት የተለቀቀውን “የስደተኛው ማስታወሻ” አነበብኩ። ሌላ ጊዜ በሰፊው ብመለስበትም አሁን ተስፋዬን አንድ ቀላል ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ። አሁን ማን ይሙት ከአስመራ ተነስተህ እስከ ናቅፋ ተራራ በደራሲ ዓይን የታዘብከው አስፋልት የሚያቁዋርጡ የደረቁ ወንዞችን ብቻ ነው? አለምክንያት በየድንጋዩ ስር ውሃ እንዳጣ ዛፍ የጠወለጉ ወጣቶችን አላየህም? ወይንስ ያንተን መምጣት አስመለክቶ እንዳታያቸው ደብቀዋቸው ነው? ብዕርህ ደፋርና ግልፅ ናት ብዬ አስብ ነበር፤ ግን የዘር ልጉዋም ሳያደናቅፋት አልቀርም።
እኔ ጨርሼአለሁ።
ነፃነትና ሰላም ለመላው አፍሪካ ህዝብ!

ኢዮብ ይስኃቅ
eyobisack@yahoo.it  

ወ/ሮ አዜብ መስፍን Azeb Mesfin