Sunday, October 27, 2013

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ ኤርትራ በተገነጠለችበት ወቅት መሆን ያለበት ይህ ነበር።

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ፡ በሊግ ኦፍ ኔሽን የሚታወቀውና፡ እንደአውሮፓ አቆጣጠር በ1961 የተባበሩት መንግሥታት ካጸደቃቸው ሦሥቱ የኤርትራ ሁኔታ ውሳኔ፡ ” ኤርትራ የፊዴሬሽኑን ሁኔታ ሕዝቡ ካልፈለገና ካርታዋ ከተገነጠለች፡ ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽን ወደሚታወቀው እዚህ ላይ ወደሚታየው ካርታዋ ይመለሳል ነበር። 
የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሽስት ወያኔ ሞተር መለስ ዘባንዳዊ፡ ወደብ ሸቀጥ ነው በሚል የብልግናና የውንብድና ንግግሩ፡ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉትን የግብር ገንዘብ ለጂቡቲ በቀን ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገብር ታውቃላችሁን? 
በውጭ ሃገር የሚገኘው ታላቁ የኢንተርኔት ሚዲያ ” ኢትዮሚዲያ ” በፊተኛው ገጹ ላይ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” በማለት ለተወናበደው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ ነው።በትክክለኛው በነአጼ ምኒልክም ይሁን በሊግ ኦፍ ኔሽን እንዲሁም የኤርትራ ፌዴሬሽን በጸደቀ ወቅት መገንጠልን ሕዝቡ የሚፈልግ ከሆነ፡ በተባበሩት መንግሥታት የሚታወቀው ይኸው ካርታ ነው። ወያኔዎች ስለድንበርም ይሁን ስለባሕር በር የመሃይማን፤ የጫካ አፈራሽ ዱርዬዎች ናቸው።
መለስ ዘባንዳዊ ወደብ ሸቀጥ ነው ብሎ ለጂቡቲ በቀን 6 ሚሊዮን ብር የኢትዮጵያ ሕዝብ የግብር ገንዘብ እንዲጠፋ ያደረገውና ኢትዮጵያን ጭለማ ያደረገው።
ታላቁ የኢትዮጵይውያን የውጭ ኢንተርኔት “፡ኢትዮሚዲያ የፊት ገጽ ላይ የተጻፈው፦ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” እውነት ነው። በወያኔ ኢትቪና ሌላችም ፕሮፓጋናዳዎች የተወናበደው በተለይም የመከላከያ ሠራዊት ነኝ ለኢትዮጵያ ቆሜያለሁ የሚል ካለ እውነታው ይኸው ነው።
Fresenay Kebede

Residents in Gambella set Indian-owned farm on fire

420013_215543375240044_2099309808_n
oct27,2013
Residents of the Gambella Regional State, Godera woreda, attacked and set the property of the Indian farm, Verdanta Harvest Plc., on fire on account of destroying the rich forest resources in the woreda where Verdanta has some 5,000 hectares for tea plantation.
According to sources in the area, the vigilantes attacked the plantation compound on Tuesday late night and set ablaze stores, fuel tankers, machineries like tractors and excavators and logs of timber, allegedly harvested from the land the company took for tea plantation. Gatlowak Tute, president of the region, confirmed the occurrence and said that a 9-man team has been sent to the area to investigate the event. “So far, security forces have taken into custody few locals suspected of involvement in the incident,” Gatlowak told The Reporter.
Verdanta took over the plantation five years ago from the Ministry of Agriculture on a 50-year lease contract with fairly cheap terms. According to the contract signed at the time, the company agreed to pay 111 birr annual lease price for the plantation extending 3012 hectares wide in Godera woreda and Gumare kebele. The total lease quotation of 16.7 million birr was agreed to be payed over the course of the 50 years at 334,332 birr per annum.
However, Verdanta requested the land for tea plantation before the ministry took over the land provision from the region and hence was able to receive 5,000 hectares although the contract with ministry say 3012. According to sources, the company have kept control of the 5,000 hectares until present, which residents of the area consider to be a forest resource and national forest region. The two kebeles of Godera woreda, Gomare and Kubu, are among the 58 primary national forest regions in the country. According to residents in the locality, the area is also rich in forest agricultural productions like honey, spice and coffee.
The vigilant residents say that the plantation company was offered is indeed a forest area that deserves to be preserved. Whereas both the regional government and the ministry say that the plot of land is no more than scattered bushes and that it does not qualify to be called a forest. According to the Food and Agricultural Organization (FAO) standards, a forest area can be referred to as such as long as it is at least half a hectare wide and have trees more than five meters tall. Residents say that even the plot that is held by the Verdanta is 5,000 hectares and that it has tree which are 10 meters tall in length. At one time former president of the republic, Girma Woldegiorgis appealed to both the ministry and the region not give the land which should be preserved as national forest area. Tea plantation require the entire vegetation to be cleared out from the area, hence the president appealed to reconsider the decision. However, both the ministry and regional administration did not want to accept the request and hence the company stayed in possession of the property until the incident.
On the other had, the widespread rumors accusing the Verdanta of harvesting timber from the forest while it was supposed to be planting tea was also not accepted by the authorities. Sources say that on quite various occasions authorities have discovered logs of timber products leaving the property of Verdanta. However, the regional president did not deny this but said that the company have has assured his administration that the timber is not for sale. Although not verified by the findings of the investigating committee yet, sources indicate that it was the vigilantes of Godera who have taken matters into their own hands.
Development Bank of Ethiopia (DBE) have provided 89.5 million birr in loans to Verdanta. Hence, some are asking if DBE collateral has been damaged in the process. Efforts to get response from the Bank was not fruitful, and other are also asking if the investigative committee could come up with an amicable solution for the residents and the company in question.

የትርፍ ሰዓት ትግል


ኢዮብ ይስኃቅ
ከዕለታት አንድ ቀን ባልተለመደ ድፍረት የሙስና ኮሚሽን ሰይፉን ትላልቅ የወያኔ ባለሥልጣናት ላይ አሳረፈ። እንደመድኃኒት ብልቃጥ እዚህም እዚያም ተወሽቆ የነበረ ብርና ንብረት እያስቆጠረ ወንጀለኞቹን ዋስ እየከለከለ ወደ ወህኒ ወረወረ። ሚኒስትሮች ከቦታቸው ተፈናቀሉ፤ የሙስና እናት የሚለውን ሜዳሊያ ያጠለቀችው ወ/ሮ አዜብ ከኤፈርት ተባረረች። ያዲሳባ ከንቲባነትም ሱሚ ነው ተባለች። ከሁለት ብቻ ሳይሆን ከብዙ ያጣች ሆነች። ህዝቡ እልል ለማለት ቢፈልግም ወያኔን ስላላመነ መጨረሻውን ለማየት መጠባበቅ ያዘ።
 የተፈራው አልቀረም ጉዱ ቀስ በቀስ ይወጣ ጀመር። በትሩ አንደኛው ጠንካራ ሙሰኛ ሌላኛውን ደካማ ሙሰኛ የሚያስገብርበት ሂደት ነበር። ህወሓትን ሊጋፋ ይችላል ተብሎ የተጠበቀው በረከት ስምኦን ጉዋደኞቹን ካስበላ በኋላ ተደራድሮ ለሌላ ሥልጣን ታጨ። ምናልባት ትግርኛ መናገሩ ከአደገኛው ሰይፍ ሳይታደገው አልቀረም – ለዛሬ።
ሰሞኑን የተስፋዬ ገብረአብ እና የተመስገን ደሳለኝ ከቅርብ ምንጮች ተገኘ ተብሎ የተጻፈውን የኢህአዴግን መበላላት የሚያሳይ ጽሑፍ ሳነብ፤ በተጨማሪ የተገነዘብኩት ነገር እስሩና መጠላለፉ ለሀገሪቱ ጥቅም ሳይሆን የወያኔን የሥልጣን ግዜ ማራዘሚያ መሆኑን ነበር። በተለይ ተመስገን አቶ ስብሃት ነጋ “በውራይና” ጋዜጣ ላይ የፃፉትን ሲያስነብበን የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር በፍፁም ሥልጣኑን የማስረከብና ለኢትዮጵያም ምንም አይነት የሚጠቅም ራዕይ እንደሌለው ያረጋገጠ ነበር። ምናልባት ራዕይ እንኳን ቢኖራቸው፤ በሥልጣን ላይ እስከነድዳቸው የመቆየት ሊሆን ይችላል። መቆየታቸው ባልከፋ! ነገር ግን ለዚች ድሃ ሀገርና ህዝብ የሚጠቅም አንድም ፖሊሲ የመቅረፅ ሃሳብ የላቸውም። እያንዳንዱ ልማት ተብዬ ከጀርባ ለነሱ ሙስና የተጋለጠ ካልሆነ በስተቀር ለሀገር ተብሎ የሚወጣ ዕቅድ የለም። ለሰው ልጅ ምን ያህል ሀብት ይበቃዋል ብለን እስክንገረም ድረስ በአጥንቱ የቀረውን ህዝብ እየጋጡት ይገኛሉ።
የመገናኛ ብዙኀኖቻችን
ባለፉት ሃያ ዓመታት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ስንመለከት በአዲስ ዘመንና አጋር የመንግሥት ሚዲያዎች እንደሚነገረን የጥጋብ ሀገር አልሆነችም። ወይንም በዘመናዊው አዲስ ዘመን “ሪፖርተር” ጋዜጣም እንደሚቀርብልን የኢትዮጵያ ችግር የጠንካራ ተቃዋሚ መጥፋት ብቻ አይደለም። ስታትስቲክ ብቻውን ዜና አይደለም ብሎ በአሉ ግርማ እንዳለን፤ የተመደበውን በጀት ድምር፣ የሚሠሩ ልማቶች ወጪና የተገኘውን ብድር በደማቅ ርዕሶች መፃፍ ብቻውን ጥሩ ጋዜጣ አያሰኝም። በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ድህነት፣ በየትምህርት ቤቱ ለሁለትና ለሦስት ቀናት እህል ባፋቸው ሳያልፍ በየክፍላቸው የሚወድቁትን ህፃናትና በየቀኑ በልማት ስም የሚፈናቀሉትን ቤተሰቦች ዜና እንደግል ጋዜጣነቱ ሲያስነብበን አናይም። አልፎ አልፎ ተኝቶ ቤቱ ድረስ የሚቀርቡለትን ትኩስ መረጃዎች ለማጀብ ቀላል ትችቶችን በርዕሰ አንቀፁ ያቀርብልናል።
እንደአለመታደል ሆኖ በሌሎችም የግል ጋዜጦች የምናገኘው ዜና ጽንፈኝነትን የተሸከመ ከመሆኑም ሌላ መንግሥትን ከመሳደብ ውጪ በተቃዋሚ ጎራ ያለውን ችግር ግልፅልፅ አድርገው አያቀርቡም። እየተሳደደም ቢሆን ሁሉንም በአንድ ሚዛን የሚያስቀምጠው አንድ ለናቱ የሆነው ተመስገን ደሳለኝ ብቻ ነው።
በሀገር ውስጥ ያለው ተቃዋሚ
በርግጥም ወደ ተቃዋሚ ጎራ ስንመጣ ቀላል የማይባል ችግር አለ። በመጀመሪያ ባገር ውስጥ ያሉትን ስንመለከት አብይ ችግር ሆኖ የምናገኘው ሥልጣንን ሙጭጭ የማለት ጉዳይ ነው። የሊቀመንበርነቱን ቦታ አስረከቡ ሲባል አረፍ ብለው ይመለሱበታል። በዚህ ሃያ ዓመት ውስጥ የትኛውም አንጋፋ ፓርቲ በአዲስ ወጣት መሪ ተተክቶ አላየንም። ተተካካን ያሉትም በአጋፋሪነት ከኋላ በምክትልነት ያስከተሉዋቸውን ሰዎች ነው። እነዚህ ሰዎች እንደአስፈላጊነቱ ቦታውን ሊለቁ የሚችሉ ታማኝ ሰዎች ናቸው። በተቃዋሚነት ዘመኑ ዲሞክራሲን ያላለማመደን መሪ በአጋጣሚ የመንግሥት ሥልጣን ቢረከብ እንዴት አይነት አምባገነን እንደሚሆን ለመገመት ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም። ለጠንቋዩ የታሰበውን እራሳችን እየበላን እራሳችን እንገምታለን።
 ስደተኛው ተቃዋሚ
ወደውጪው ተቃዋሚ ስንመጣ ሰሞኑን “ሰላቢ ፀሐፊዎች” በሚል በተስፋዬ ገብረአብ የቀረበውን ጽሑፍ በማስታወስ ነው። ተስፋዬ ይህን ያለው በብዕር ስም ጎርፍ የሚለቁትን ፀሐፊዎች ለመንካት ነው። እኛ ደግሞ ሰላቢ ፖለቲከኞች እንላለን – ቁርጠኝነት ጎሎዋቸው የሌላውን የትግል ስሜት ይሰልባሉና። በትክክል የምንስማማበት አንድ ነጥብ አለ። ይኸውም ኢትዮጵያ ፋታ በማይሰጥ አጣብቂኝ ውስጥ እንዳለች። ይህ ማለት ማቄን ጨርቄን ሳንል የምናምንበትን ወይም የምንሰብከውን ትግል መከተል ይሆናል። ወድድንም ጠላንም የዛሬዎቹ መሪዎች በረሃ በገቡበት ወቅት ወጣትነታቸውን ጨምሮ ብዙ ጥቅሞቻቸውን መስዋዕት አድርገው ነው።
ለምሳሌ መለስን እና ኢሳያስ አፈወርቂን ብንወስድ፤ አንዳቸው የተከበረ ዶክተር፣ ሌላኛቸው ደግሞ ኢንጅነር የመሆን ተስፋ የነበራቸው ወጣቶች ነበሩ። በሀብትም ቢሆን ደጃዝማች አባቶቻቸው መሶባቸው ሙሉ፣ ጎተራቸው ካመት ዓመት የማይጎድል ባላባቶች ነበሩ። ጥሩ ኑሯቸውንና የነገ ትልቅ ሰው የመሆን ዕድላቸውን በሳጥን ቆልፈውበት ነው ወደ በረሃ የገቡት። አይ! አሸንፈው መሪ ለመሆን ነው የሚል የዋህ ያለ አይመስለኝም። ኃይለሥላሴም ሆኑ ደርግ ይወድቃሉ ብሎ እንኳን ሰዉ እግዜሩም እርግጠኛ የነበረ አይመስለኝም። የራሱን ጀግኖች እየበላ መንገዱን ጠርጎ ያስገባቸው ወደድንም ጠላንም ኮሌኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ነው።
ይህ እንዲህ ሆኖ ሳለ የዛሬዎቹ ተቃዋሚዎች በተለይ ደግሞ ብቸኛው አማራጭ የትጥቅ ትግል ነው የሚሉት፣ እንኳን ሕይወታቸውን፣ ደሞዛቸውን ሲሰዉ አናይም። ኢትዮጵያ ያለችበት ችግር አጣዳፊና ግዜ እንደማይሰጥ ከተስማማን ፈጣን እርምጃ መወሰድ ነበረበት። ከዚህ ይልቅ መግለጫዎችን በመስጠቱ ላይና ገቢ ማሰባሰቡ ላይ በርትተው ሲንቀሳቀሱ እያየን ነው።
ከጥቂት ዓመታት በፊት በድል ማግስት አዲስ አበባ የሚያስገባ ካርድ በገንዘብ የሚታደልበት ዝግጅት ተደርጎ ነበር – በግንቦት ሰባት። በዚህ አጭር ጊዜ ወያኔ ወድቆ አዲስ አበባ ይያዛል የሚል የየዋህ ግምት ባይኖረኝም በኢትዮጵያ ተራሮችና ጫካዎች ውስጥ እየተሽሎከለከ ወያኔን የሚያሸብር ታጋይ መጠበቄ አልቀረም። በኢንተርኔት መስኮቶች ወዛቸው ግጥም ያለ ባለስካርፍ ታጋዮችን ተመልክተናል። ግን የዋሉበትን የትግል አውድማ በስህተት እንኳን ሰምተን ወይንም አይተን አናውቅም።
አንድ እየተሠራ ያለ ነገር ቢኖር ይሔ እንደጉድ ድህነትንና ግፍን እየሸሸ በረሃና ባህር የሚበላው ወጣትና ወደ ዐረብ ሀገር የሚሰደዱ እህቶች ምርጫቸው ሽሽት ሳይሆን የችግሮቻቸው ምንጭ የሆነውን መንግሥት ለመጣል ትግሉን መቀላቀል ነበር። ይህ መሆኑ ቀርቶ ግን በኢትዮጵያ ጫካዎች ልናያቸው የሚገቡ ወታደራዊ ልብሶች እንደእንቁጣጣሽ ቀሚስ እነታማኝ በየነን በፈንድሻ ለመቀበል በየስደቱ መድረክ ላይ ሲጌጥባቸው እናያለን።
 ኢትዮጵያን ከህወሓት ጥፋት ለማዳን ያለን ምርጫ
ሀገራችን በህወሓት መራሹ መንግሥት እጅ ከቆየች ያለማጋነን በሚቀጥሉት ዓመታት ዛሬ ያለችበት ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንደማይኖራት ማወቅ አለብን። ህዝቡም በዘርና በኃይማኖት ተከፋፍሎ እርስ በእርሱ የሚበላላባት ምድር ትሆናለች። ስለዚህም የትርፍ ጊዜ (part time) ትግል ለዚች ሀገር እንደማይመጥን አውቀን የመረጥነውን የትግል መስመር በቁርጠኝነት መቀጠል አለብን። በሰላማዊ ከሆነ በሰላማዊ፣ በትጥቅ ትግል ከሆነ በቦታው እታች ወርዶ መታገል ያስፈልጋል። ይህ ካለሆነ ግን የቁርጠኛ ልጆችን መንገድ በመሪነት ስም በመዝጋት በእጅ አዙር የወያኔ መንግሥት ዕድሜ እንዲራዘም ማገዝ አይገባም።

ትንሽ መልዕክት ለተስፍሽ (ተስፋዬ) ገብረአብ
በመጨረሻ ከላይ ስሙን ለጠቀስኩት ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ የምለው አንድ ወንድማዊ ምክር አለ። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ አሁን በቅርብ ደግሞ ለላይፍ መጽሔት በሰጠው ቃለመጠይቅ ስለኤርትራ ለምን እንደማይፅፍ ተጠይቆ “ሰዎች የማላውቀውን እንድጽፍ ለምን ይጠብቃሉ” የሚል መልስ ሰጥቷል። ወይንም በሚቀጥለው መጽሐፉ በአንዲት ምዕራፍ እንደሚያወጋን ተናግሯል። እኔ ግን የቡርቃ ዝምታን የሚያክል መጽሐፍ ለመጻፍ አርባጉጉ ወይ በደኖ ካሳለፈው ጊዜ የበለጠ በኤርትራ ቆይቶዋል የሚል ግምት አለኝ። በእናቱ ኤርትራዊ ቤተሰብ ውስጥ ማደጉ የኤርትራዊያንን ሕይወትና ኑሮ ከሌላው ሰው በተሻለ የማወቅ ዕድሉ አለው። ለአንድ አይደለም ለዕድሜ ልኩ የሚበቃ መጽሐፍ የሚወጣው ግፍ በኤርትራ ምድር እየተፈጸመ ነው። ተስፍሽ ደራሲ ድንበር እንደማይወስነው ላንተ መንገር የለብኝ። ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለህ ማመንህም ቢሆን ስለጎረቤት ሀገር ህዝብ መበደል ስለመጻፍ ሊገታህ አይገባም። ብዕርህ ስለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ስለመላው አፍሪካ ህዝብ መዘመር ይገባታል።
ይህቺን ትንሽ ጽሑፍ ከጫርኩ በኋላ በኢንተርኔት የተለቀቀውን “የስደተኛው ማስታወሻ” አነበብኩ። ሌላ ጊዜ በሰፊው ብመለስበትም አሁን ተስፋዬን አንድ ቀላል ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ። አሁን ማን ይሙት ከአስመራ ተነስተህ እስከ ናቅፋ ተራራ በደራሲ ዓይን የታዘብከው አስፋልት የሚያቁዋርጡ የደረቁ ወንዞችን ብቻ ነው? አለምክንያት በየድንጋዩ ስር ውሃ እንዳጣ ዛፍ የጠወለጉ ወጣቶችን አላየህም? ወይንስ ያንተን መምጣት አስመለክቶ እንዳታያቸው ደብቀዋቸው ነው? ብዕርህ ደፋርና ግልፅ ናት ብዬ አስብ ነበር፤ ግን የዘር ልጉዋም ሳያደናቅፋት አልቀርም።
እኔ ጨርሼአለሁ።
ነፃነትና ሰላም ለመላው አፍሪካ ህዝብ!

ኢዮብ ይስኃቅ
eyobisack@yahoo.it  

ወ/ሮ አዜብ መስፍን Azeb Mesfin

Monday, October 14, 2013

ወያኔ አንዳንድ የአማራ ክልል ከተሞችን ለራሱና ለሌሎች ለአጎራባች ክልሎች ሊሸልም መሆኑ ተሰማ

ከዚህ ቀደም ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ገንጥሎ ትግራይ ዉስጥ የጨመረዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ያኔ የዘረፈዉ መሬት አልበቃ ብሎት አሁንም በአማራ ክልል የሚገኙ አንዳንድ የድንበር ከተሞችን ወደራሱ ወይም (ትግራይ ክልል) ለመጨመር ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ኢሰት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። የኢሳት ዘገባ በግልጽ እንዳስቀመጠዉ በድንበር አካባቢ የሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች የሚሰጡት ለኢያንዳንዱ አጎራባች ክልል ቢሆንም ወያኔ ይህንን የአማራን ክልል ከተሞች ለአጎራባች ክልሎች ሁሉ የማሸጋሸግ ዕቅድ ያወጣዉ ለይስሙላ እንደሆነና ዋና አላማዉ አማራዉን ለማዳከምና የራሱን ክልል ለማስፋት ነዉ የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። በድንበር አካባቢ ከሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች አስተዳዳሪዎች በተገኘው መረጃ መሰረት የጃን አሞራ፣ የማይጸብሪ ፣ የራስዳሸንና የአዲአርቃይ አካባቢዎች ትግራይ ክልል ዉስጥ የሚጠቃሉ ሲሆን በመተማ በኩል ደግሞ የተወሰነውን ክፍል ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመስጠት ድርድር በመካሄድ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የየከተማዎቹ ባለስልጣናት ለኢሳት በሰጡት መረጃ መስረት ባለስልጣናቱ የህዝቡን የልብ ትርታ አዳምጠዉ የህዝብን ሀዘንና ድንጋጤ የተመለከቱ ሲሆን፣ አንዳንድ የወረዳ ባላስልጣናት ደግሞ የችግሩን ስፋት ኢሳት ለህዝብ ይፋ እንዲያሳዉቅላቸዉ ተማጽነዋል። የወያኔ አገዛዝ ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ስር የነበረውን የመተከል ዞን ለቢኒሻንጉል ጉምዝ ፤ራያና ቆቦን ፤ዳንሻንና ሁመራን በመተማ በኩል ለሱዳን ፤ቀሪውን የመተማ ክፍል ደግሞ ለቤንሻንጉል መሰጠቱን በማውሳት ፣ አሁንም ተጨማሪ መሬት እየተቆረሰ ክልሎችን ለማስደሰት ሲባል ብቻ እኛን እየተጎዳን ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የአንቀጽ 39 ትሩፋቶች የሰጡን ገፀ በረከቶች ናቸው ሲሉ ያማረሩት የድንበር ከተማ ነዋሪዎች ደግሞ ”ጨለምተኛ አባት መሬት እየሸጠ ልጆቹን ርስት ያሳጣል፡፡ ጨለምተኛ መንግስት ደግሞ አገርን በመሸጥ ዜጎችን ያስደፍራል፡፤ ማንነታቸውን ያሳጣል፤ መንግስትም ማንነታችንን እየነጠቀን ነው ሲሉ” በወያኔ አገዛዝ ላይ ያላቸዉን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁኔታው ያበሳጫቸው ነዋሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ድርጅቶች ጉዳዩን አጽንኦት ሰጥተው ሊያዩት ይገባል ብለዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ የትግርኛን ቋንቋ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንዲማሩት ለማድረግ ታስቦ በጎንደር በተካሄደው ፓይለት ጥናት ህዝባዊ ተቃውሞ በማስነሳቱ እንዲቆም ተደርጓል። ይህንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ጥናት ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ባየ ይማም በቅርቡ በአቀረቡት ጥናት የመንግስት ቋንቋ አጠቃቀም ‘የህዝብን ጉዳይ በህዝብ ቋንቋ’ የሚለውን መርህ የተከተለ ባለመሆኑ ህዝቡ ማግኘት ያለበትን መልእክት በትክክል እያገኘ፤ ለለውጥም እየተነሳሳ አይደለም ብለዋል፡፡ ባጭር ቃል በዚህ አይነት ቋንቋ የሕዝብን አእምሮ መቀየር እንደማይቻል የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ባለስልጣናቱ የአማረኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የበኩላቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል፡፡“ሀገራችን የቋንቋ ፖሊሲና የአጠቃቀም ደንብ ወይም ስርዓት እስካሁን የላትም፡፤ እስካሁን ድረስ ከህገመንግስታዊ የመብት ማረጋገጫ አንቀጾች ያለፈ፣ ቋንቋን እንደ ማንኛውም የሀገር ሀብት በእቅድ የሚያሳድግ፣ የሚቆጣጠር፣ አጠቃቀሙን ስርዓት የሚያሲይዝ ፖሊሲና ዝርዝር ደንብ የለንም፡፡ ባለመኖሩም ሁሉም እንደፈለገ የሚተረጉምበት፣ የሚጽፍበት፣ የሚያሰራጭበት ሁኔታ ውስጥ ገብተናል፡፡ ይህ ሊቆምና ቋንቋዎቻችን በዕቅድ ሊያድጉና ጥቅም ላይ ሊውሉ ይገባል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
የአማርኛ ቋንቋ የሀገሪቱ የስራ ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ክልሎች በፍፁም ጥላቻ እንዲመለከቱትና እንዲሁም ክፍል ውስጥ ገብተው የመማርን መብት ለተወላጆች ብቻ ትቻለሁ በማለት የአማርኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ፤ በትግራይ ፤ በኦሮምያና ደቡብ ክልሎች ክፍት እንደሚሆኑ ታዉቋል። ተማሪዎች በቋንቋ ትምህርት በሚመዱበበት ወቅትም በአማርኛ ቋንቋ የሚሰጡ ደጋፊ ትምህርቶችን ላለመማር አሰጣ አገባ እንደሚገቡ ታውቋል፡፡በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በቤንሻንጉል እና ሶማሌ ክልሎች የክልሎቹን ቋንቋ የማይናገሩ ተማሪዎች ተመርቀው ስራ ለማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ከአማራ ክልል የሚመጡ ተማሪዎች ከክልላቸው፣ ከአዲስ አበባ እና ከደቡብ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች ተቀጥረው ለመስራት እየተቸገሩ ነው።አንዳንድ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት ካልሆነ በስተቀር የአማራ ክልል ተማሪዎች ስራ ለመያዝ እንደሚቸገሩ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል። በሌላ በኩል ግን አማርኛ የሚችል የማንኛውም ክልል ተወላጅ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ስራ የመያዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ወያኔ አንዳንድ የአማራ ክልል ከተሞችን ለራሱና ለሌሎች ለአጎራባች ክልሎች ሊሸልም መሆኑ ተሰማ

ከዚህ ቀደም ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ገንጥሎ ትግራይ ዉስጥ የጨመረዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ያኔ የዘረፈዉ መሬት አልበቃ ብሎት አሁንም በአማራ ክልል የሚገኙ አንዳንድ የድንበር ከተሞችን ወደራሱ ወይም (ትግራይ ክልል) ለመጨመር ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ኢሰት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። የኢሳት ዘገባ በግልጽ እንዳስቀመጠዉ በድንበር አካባቢ የሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች የሚሰጡት ለኢያንዳንዱ አጎራባች ክልል ቢሆንም ወያኔ ይህንን የአማራን ክልል ከተሞች ለአጎራባች ክልሎች ሁሉ የማሸጋሸግ ዕቅድ ያወጣዉ ለይስሙላ እንደሆነና ዋና አላማዉ አማራዉን ለማዳከምና የራሱን ክልል ለማስፋት ነዉ የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። በድንበር አካባቢ ከሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች አስተዳዳሪዎች በተገኘው መረጃ መሰረት የጃን አሞራ፣ የማይጸብሪ ፣ የራስዳሸንና የአዲአርቃይ አካባቢዎች ትግራይ ክልል ዉስጥ የሚጠቃሉ ሲሆን በመተማ በኩል ደግሞ የተወሰነውን ክፍል ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመስጠት ድርድር በመካሄድ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የየከተማዎቹ ባለስልጣናት ለኢሳት በሰጡት መረጃ መስረት ባለስልጣናቱ የህዝቡን የልብ ትርታ አዳምጠዉ የህዝብን ሀዘንና ድንጋጤ የተመለከቱ ሲሆን፣ አንዳንድ የወረዳ ባላስልጣናት ደግሞ የችግሩን ስፋት ኢሳት ለህዝብ ይፋ እንዲያሳዉቅላቸዉ ተማጽነዋል። የወያኔ አገዛዝ ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ስር የነበረውን የመተከል ዞን ለቢኒሻንጉል ጉምዝ ፤ራያና ቆቦን ፤ዳንሻንና ሁመራን በመተማ በኩል ለሱዳን ፤ቀሪውን የመተማ ክፍል ደግሞ ለቤንሻንጉል መሰጠቱን በማውሳት ፣ አሁንም ተጨማሪ መሬት እየተቆረሰ ክልሎችን ለማስደሰት ሲባል ብቻ እኛን እየተጎዳን ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የአንቀጽ 39 ትሩፋቶች የሰጡን ገፀ በረከቶች ናቸው ሲሉ ያማረሩት የድንበር ከተማ ነዋሪዎች ደግሞ ”ጨለምተኛ አባት መሬት እየሸጠ ልጆቹን ርስት ያሳጣል፡፡ ጨለምተኛ መንግስት ደግሞ አገርን በመሸጥ ዜጎችን ያስደፍራል፡፤ ማንነታቸውን ያሳጣል፤ መንግስትም ማንነታችንን እየነጠቀን ነው ሲሉ” በወያኔ አገዛዝ ላይ ያላቸዉን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁኔታው ያበሳጫቸው ነዋሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ድርጅቶች ጉዳዩን አጽንኦት ሰጥተው ሊያዩት ይገባል ብለዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ የትግርኛን ቋንቋ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንዲማሩት ለማድረግ ታስቦ በጎንደር በተካሄደው ፓይለት ጥናት ህዝባዊ ተቃውሞ በማስነሳቱ እንዲቆም ተደርጓል። ይህንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ጥናት ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ባየ ይማም በቅርቡ በአቀረቡት ጥናት የመንግስት ቋንቋ አጠቃቀም ‘የህዝብን ጉዳይ በህዝብ ቋንቋ’ የሚለውን መርህ የተከተለ ባለመሆኑ ህዝቡ ማግኘት ያለበትን መልእክት በትክክል እያገኘ፤ ለለውጥም እየተነሳሳ አይደለም ብለዋል፡፡ ባጭር ቃል በዚህ አይነት ቋንቋ የሕዝብን አእምሮ መቀየር እንደማይቻል የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ባለስልጣናቱ የአማረኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የበኩላቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል፡፡“ሀገራችን የቋንቋ ፖሊሲና የአጠቃቀም ደንብ ወይም ስርዓት እስካሁን የላትም፡፤ እስካሁን ድረስ ከህገመንግስታዊ የመብት ማረጋገጫ አንቀጾች ያለፈ፣ ቋንቋን እንደ ማንኛውም የሀገር ሀብት በእቅድ የሚያሳድግ፣ የሚቆጣጠር፣ አጠቃቀሙን ስርዓት የሚያሲይዝ ፖሊሲና ዝርዝር ደንብ የለንም፡፡ ባለመኖሩም ሁሉም እንደፈለገ የሚተረጉምበት፣ የሚጽፍበት፣ የሚያሰራጭበት ሁኔታ ውስጥ ገብተናል፡፡ ይህ ሊቆምና ቋንቋዎቻችን በዕቅድ ሊያድጉና ጥቅም ላይ ሊውሉ ይገባል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
የአማርኛ ቋንቋ የሀገሪቱ የስራ ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ክልሎች በፍፁም ጥላቻ እንዲመለከቱትና እንዲሁም ክፍል ውስጥ ገብተው የመማርን መብት ለተወላጆች ብቻ ትቻለሁ በማለት የአማርኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ፤ በትግራይ ፤ በኦሮምያና ደቡብ ክልሎች ክፍት እንደሚሆኑ ታዉቋል። ተማሪዎች በቋንቋ ትምህርት በሚመዱበበት ወቅትም በአማርኛ ቋንቋ የሚሰጡ ደጋፊ ትምህርቶችን ላለመማር አሰጣ አገባ እንደሚገቡ ታውቋል፡፡በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በቤንሻንጉል እና ሶማሌ ክልሎች የክልሎቹን ቋንቋ የማይናገሩ ተማሪዎች ተመርቀው ስራ ለማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ከአማራ ክልል የሚመጡ ተማሪዎች ከክልላቸው፣ ከአዲስ አበባ እና ከደቡብ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች ተቀጥረው ለመስራት እየተቸገሩ ነው።አንዳንድ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት ካልሆነ በስተቀር የአማራ ክልል ተማሪዎች ስራ ለመያዝ እንደሚቸገሩ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል። በሌላ በኩል ግን አማርኛ የሚችል የማንኛውም ክልል ተወላጅ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ስራ የመያዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

Sunday, October 13, 2013

በጎንደር ከተማ ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት ሞተው መገኘታቸው ከቦታው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል፣



October 13, 2013

በደረሰን ዘገባ መሰረት በጎንደር ከተማ በተለምዶ አራዳ አየተባለ በሚጠራው አክሱም ሆቴል አከባቢ መስከረም 26,2006 ዓ/ም ሌሊት ገዳያቸው ያልታወቁ ምክትል ሳጅን ይፍጠር ዓሊና ምክትል ሳጅን ደምመላሽ ይርዳው የተባሉ ሁለት የፌደራ ፖሊስ አባላት ሞተው ተገኝተዋል፣ ከሟቸቹ አንዱ በጩቤ ተወግቶ የተገደለ ሲሆን በሁለተኛው ላይ በዓይን የሚታይ አካላዊ ጉዳት አልነበረውም፣ ታጥቀውት የነበረውንም ትጥቅ በገዳዮቹ መወሰዱን ቷውቋል፣ በስርዓቱ የፌደራል ፖሊስ አባላት የሚደርሰው ጥቃት በሁሉም የሃገሪቱ ከተሞች የሚታይ ሲሆን በጎንደር ከተማ በሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት የደረሰውን ግድያ በIህአዴግ ስርዓት በተማረሩ የስርዓቱ ኗሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አይቀርም የሚል ጥርጣሬ በከተማዋ በሰፊው ይወራል::

Source : TPDM

ETV በቦሌ አዲስ አበባ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን ዘገበ

ዘገባው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የተቀነባበረ ይሁን አይሁን በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠ የETV ዘገባ እንደወረደ 
እሁድ 3 2006 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የቤት ቁጥር 2333 ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሁለት ግለሰቦች ተከራይተው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ ጸረ ሽብር ሀይል ገለጸ፡፡
በፈንጂ ፍንዳታው ሁለቱ ግለሰቦች ህይወታቸው አልፏል፡፡
ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን የገለጸው ግብረሀይሉ በምርመራ የደረሰበትን ውጤትም በቅርቡ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል፡፡
ህብረተሰቡ ቤት እና መኪናዎችን በሚያከራይበት ወቅት የተከራዮችን ማንነት ከማወቁም ባሻገር ለፖሊስ እና ለጸጥታ ሀይሎች ማሳወቅ እንዳለበት ግብረሀይሉ አሳስቧል፡፡

የኢህአዴግ አፈና አሁንም እንደቀጠለ ነው!! (ጥቅምት 2 ቀን 2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት)

ሰማያዊ ፓርቲ ለጽ/ቤት መጠቀሚያ ተከራይቶ ነበረውን ቢሮ በግድ ካልወጣችሁ ሲሉ ከነበሩት የጉለሌ ክ/ከተማና ወረዳ 03 ካድሬዎች መካከል በተነሳው ውዝግብ መፍትሄ ለማፈላለግ መሀከል የገባው የመነን አካባቢ ፖሊስ በውይይት ለመፍታት ሁለቱም አካላት ከቤቱ እንዲወጡና ፖሊስ ቤቱን እንዲጠብቅ፤ በቀጣዩ ቀን ለመነጋገር ስምምነት ተይዞ የፓርቲው አባላት ወደቤታቸው ለመሄድ ከጽ/ቤቱ ለቀው ቢሄዱም ከመንገድ ላይ
1.ወ/ት ሀና ዋለልኝ (የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ)
2.አቶ ዮናስ ከድር (የምክር ቤት አባል)
3.ወ/ት እየሩስ ተስፋው
4.አቶ ዮናታን ተስፋዬ
5.አቶ አቤል ኤፍሬም
6.አቶ አህመድ መሀመድ
7አቶ እያስፔድ ተስፋዬ
የአራዳ ክ/ከተማ ፖሊስና የደህንነት አካላት ወደ ጃልሜዳ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸው አሁን በደረሰን መረጃ ማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ በፊት እንደሚታወሰው የጃልሜዳ አካባቢ ፖሊስ የፓርቲውን አባላት እያሰረ ይደበድብ እንደነበረ ፤ አሁንም ከአንድ ሰአት በላይ አባሎቹን ምን እያደረጋቸው እንደሆነ ማወቅ አለመቻሉ እየተደበደቡ ይሁን? የሚለውን ስጋት በከፍተኛ ሁኔታ አጭሯል፡፡

Monday, October 7, 2013

በጣሊያኑ የባህር አደጋ የሞቱት የ153 የኢትዮጵያውያን እና የኤርትራውያን ስም ዝርዝር

italy
ሰሞኑን ከሊቢያ ተነስተው በጣሊያን ባህር አቅራቢያ ባህር ውስጥ ጠልቀው ከሞቱት ወገኖች ውስጥ በተለያዩ ሚዲያዎች የኤርትራ ስደተኞች ብቻ እንደሞቱ እየተዘገበ ነው። ዘ-ሐበሻ ግን የኤርትራ ስደተኞች መባሉን አታምንብተም። የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሔኖክ ዓለማየሁ በሊቢያ ስደት ውስጥ ያሳለፈ በመሆኑና ወደጣሊያንም በባህር ለመሻገር ሞክሮ በእስር ምክንያት ሕይወቱ በመትረፉ ዛሬ የኤርትራ ስደተኞች ብቻ ሕይወታቸው እንዳለፈ ተደርጎ መወራቱን አይቀበለውም። በሊቢያ ቤንጋዚ፣ ትሪፖሊ፣ ኩፍራ፣ ኢጅዳቢያና ሌሎችም እስር ቤቶች በርካታ ከምስራቅ አፍሪካ ወደ ጣሊያን ለመሰደድ ሄደው የታሰሩ ሰዎች ከዘ-ሐበሻ አዘጋጅ ጋር የታሰሩ ነበሩ። እነዚህ ዜጎች በተለይም ኢትዮጵያውያኑ እስር ቤት ሲገቡ ዜግነታቸውን ‘ኤርትራዊ እንደሆኑ እንዲናገሩ” አሻጋሪዎች ይነግሯቸዋል። ምክንያታቸውም የሊቢያ መንግስት እስር ቤት ውስጥ ኢትዮጵያዊ ነኝ ያለን ወደ አዲስ አበባ ስለሚሸኘው፤ ኤርትራዊ ነኝ የሚል ግን ወደ አስመራ ስለማይላክ ሁሉም ኢትዮጵያዊም ኤርትራዊም “ኤርትራዊ ነኝ” ብሎ ነው የሚገልጸው። አሁንም የሆነው ያ ነው። ኤርትራዊያን ናቸው ከተባሉት ውስጥ አብዛኛው ኢትዮጵያውያንም ጭምር ናቸው በሚል ዘ-ሐበሻ ታምናለች።
የሞቱትን ነብሳቸውን ይማረው፡ የሟቾች ዝርዝር የሚከተለው ነው፡

ኤርትራ በኢትዮጲያ መከላከያና ደህንነት ውስጥ ሰላዮችን ማሰማራቷን ኢትዮጲያ አመነች፥ ኢሳት ዜና

October 4, 2013
The charges under the files Fikru Abebe Haile, Tesfu Abate Abyneh, Mohmamed Umer Mohammed, Tamene  Tememte Zewde and Zerfu Melka, members of the Ethiopian Defense Forces, and accused of spying for Eritrea, reads that theEthiopian government has admitted that it has been infiltrated by the Eritrean IntelNetwork built between Addis Abeba, Borena and Nairobi, Kenya, ESAT has reported tonight.
The dossier that ESAT has accessed also states that Getachew Assefa, Head of the Ethiopian Intel, had told Intel members on a February 26, 2012 meeting that they had collected public opinion if they should go to war with Eritrea and the public’s response was against the idea. The details of this meeting were sent to Eritrea.
ESAT also reported that the dossier shows that the Ethiopian government has no interest of going into war with Eritrea but wanted to wipe out Ethiopian rebels that came from Eritrea through the North Western border of EthiopiaHumera and decided to weaken local opposition parties before the next election, 2015.
Listen to ESAT’s extended reportage here

Monday, September 16, 2013

734 ሚሊዮን 600 ሺ ብር የመዘብሩ የስራ ሃፊዎች አለመቀጣታቸውን መረጃዎች አመለከቱ

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን የተገኝው መረጃ እንደሚያመለክተው ከተለያዩ የፌደራል መስሪያ ቤቶች 734 ሚሊዮን 6 መቶ ሺ ብር የመዘብሩ የስራ ሃፊዎች በተጣራ መረጃ ክስ ቢመሰረትባቸውም የውሳኔ ቅጣት እንዳልተላለፈባቸው ታውቋል።
ለረጅም ጊዜ በተደረገ ምርመራ ተጣርቶና መስረጃ ተገኝቶባቸው ከ2004 ዓም ጀምሮ ክስ የተመሰረተባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች የውሳኔ ሀሳብ እንዳልተላለፈባቸው ከመሰሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ላይ  94 ሚሊዮን 300 ሺ ብር  ከትምህርት ተቋማት ግንባታ ጋር በተያያዘ የተፈጸመ የሙስና ወንጀል ምርመራ ተጠናቆ ክስ ቢመሰረትም በቂ ውሳኔ ሳያገኝ ቀርቷል።
ከአራዳ ክ/ከተማ መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ  ህገወጥ የካሳ ክፍያ በመፈጸሙ ሦስት የምርመራ መዝገቦች ተጠናቀው በ2004 ዓ.ም ክስ ቢመሰረትም የቅጣት ውሳኔ አላገኝም።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀራጅ ሽያጭ ጋር በተያያዘ የ12 ሚሊዮን ብር እና የ34 ሚሊዮን ብር ህገወጥ ብድርን እንዲፈፀም ያደረጉ አካላት በቂ የሰነድ ማስረጃ እንደተገኘባቸው ቢገለጽም እርምጃ ሳይወሰድ ቀርቱዋል፡፡
በቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ከመመሪያና አሰራር ውጪ ለግለሰቦች የስልክ መስመር እንዲዘረጋ በማድረግ በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር ስልክ በማስደወል በመስሪያ ቤቱ ላይ 14 ሚሊዮን ብር ጉዳት መድረሱን የተመለከተ  ሁለት ምርመራዎች ተጠናቀው በክስ ሂደት ላይ ሲሆኑ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በሚፈጥሩት ጫና ክሱ እየተጓተተ ነው።
በትግራይ ክልል የሚገኘው በሼባ የብረታ ብረት ማቅለጫ ፋብሪካ ለፋብሪካው የተዘረጋው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ቆጣሪ መሳሪያ ሥራውን በአግባቡ እንዳይሰራ በማድረግ መብራት ሀይል ከሽያጭ ማግኘት ይገባው የነበረውን ገቢ በማስቀረት በአገር ላይ  65 ሚሊዮን 300 ሺ ጉዳት በመድረሱ ምርመራው ተጣርቶ ለወሳኝ አካል ቢተላለፍም ውሳኔ ሳያገኝ ቀርቷል።
በተመሳሳይ በኦሮምያ ክልል በደብረዘይት የሚገኝ የግል የብረታ ብረት ማቅለጫ ፋብሪካ ለፋብሪካው የተዘረጋው የኤሌክትሪክ ፍጆታ ቆጣሪ መሳሪያ ሥራውን በአግባቡ እንዳይሰራ በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ከሽያጭ ማግኘት ይገባው የነበረውን ገቢ በማስቀረት በአገር ላይ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረሱ ምርመራው አጣርቶ የፀረ ሙስና ኮሚሺን ቢልክም የፍትህ መጓተት ታይቶበታል።
በመብራት ሀይል አላግባብ በ 248 ሚሊዮን 900 ሺ ብር የተፈጸመ የ4 ሺ4 መቶ 70 ትራንስፎርመሮች አለም አቀፍ ግዢ በሁለት የምርመራ መዝገቦች የተጣራ ቢሆንም ውሳኔ አልተሰጠበትም።
ንብረቱ የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የብረት ማኑፋክቸሪንግ ማሽን ግንባታ ኢንዱስትሪ የሆነ ግምቱ  4 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ የሆነ የብርና የነሃስ ሜዳልያ ከግምጃ ቤት በመጥፋቱ ተመርምሮ የተረጋገጠ ቢሆንም ውሳኔ አላገኘም።
በተንዳሆ ፕሮጀክት ከግብር ጋር በተያያዘ በመንግስት ላይ     ጉዳት በመድረሱ ምርመራው ተጠናቆ ክስ ተመስርቷል። በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ በሊዝ እንዲስተናገድ የተወሰነለትን የመኖሪያ ቤት ኅ/ሥ/ማ ያለ ሊዝ በማስተናገድ የተሰጠ 30 ሺ 3 መቶ 32 ካ/ሜ ቦታ ምርመራ ተጠናቆ ክስ የተመሰረተ ቢሆንም ውሳኔ አላገኘም።
ለብሄራዊ ባንክ በሽያጭ ከሚቀርብ ወርቅ ጋር በተያያዘ የባንኩ ሰራተኞችና ነጋዴዎች በመመሳጠር 63 ሚሊዮን ብር በመመዝበር አስቀድሞ ተከሰው የነበሩ አሁን ጥፋተኛ ተብለው ጉዳዩ ለቅጣት ውሳኔ ተቀጥሯል።
በቂርቆስ ክ/ከተማ በልማት ተነሺዎች ስም ከመመሪያ ውጪ ግምቱ 13 ሚሊዮን 3 መቶ ሺ የሆነ 2, ሺ 1 መቶ 45 ካ/ሜትር ትርፍ መሬት አላግባብ በተሰጣቸው እና ከካሳ ክፍያም ጋር በተያያዘ  5 ሚሊዮን 2 መቶ ሺ ብር በትርፍ የተከፈላቸው ግለሰቦች ጉዳይ፤ በኢትዮጵያ የመድሃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ሀዋሳ ቅርንጫፍ በእምነት ማጉደል ወንጀል ግምቱ ብር 1 ሚሊዮን 7 መቶ ሺ የሆነ መድሃኒት ተመዝብሮ ለግል ጥቅም መዋሉ እና በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በተደረገ የ100 ሚሊዮን የእህል ግዢ ጨረታ ግለሰቦች ሀሰተኛ ሰነድ በማቅረብ ጨረታውን ያሸነፉ መሆኑ በተደረገው ምርመራ በመረጋገጡ ጨረታው እንዲሰረዝና በግለሰቦቹ ላይ ክስ እንዲመሰረት የተደረገባቸው በጥቅሉ ከህዝብ በግብር የተሰበሰበ በርካታ ገንዘብ በአንድም በሌላ መልኩ በከፍተኛ አመራሮች ተጽእኖ በ2004 እና በ2005 ዓ.ም ተጣርቶ ለፍርድ ሰጭው አካል ቢተላለፍም ውሳኔ ሳይሰጥባቸው ቀርተዋል፡፡
ከ 7 መቶ ሚሊዮን  ብር በላይ የመዘበሩ የስራ ሃፊዎች አልተቀጡም ሲል ከፀረ ሙስና ኮሚሺን የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡ አሀዙ በ2005 የተፈጸመውን ሙስና አላካተተም።
ባለፉት 22 የኢህአዴግ የአገዛዝ አመታት የተፈጸሙና በጸረ ሙስና ኮሚሽን ያልተጣራ በሙስና የተዘረፈ ገንዘብ በቢሊዮኖች እንደሚቆጠር ይገመታል።

በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ተጠየቀ።



ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና ሌሎች በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ተጠየቀ።
መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከዓመት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ለ14 ወራት በቃሊቲ እስርቤት ከታሰሩ በኋላ ተፈተው የወጡት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ማርቲን ሺቢ እና ዩዋን ፐርሹን እንዲሁም ዓለምዓቀፍ የሰብዓዊና የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተወካዮች፡ ጋዜጠኞችና በስዊድን የሚኖሩ በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ስዊድናውያን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባዘጋጀው ደብዳቤ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የታሰሩ ጋዜጠኞችን እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ኢትዮጵያ ውስጥ ያሳለፉትን የእስር ህይወት የሚተርከውን እና በቅርቡ ለህትመት የበቃው 438ቱ ቀናት የሚለው መጽሃፋቸው ኢትዮጵያውያንን የህሊና እስረኞችን ለማስታወስ በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ይፋ እንዲሆን የወሰኑት በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው በከፍተኛ ስቃይ ለሚንገላቱት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች እና ሌሎች የህሊና እሰረኞች የገቡትን ቃል ለማደሰ እንደሆነ በዝግጅቱ ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
በአሸባሪነት ተወንጅለው በእስር ላይ የሚገኙ የስራ ባልደረቦቻቸው በዓለም ዓቀፉ ሚዲያ በመዘንጋታቸው እና ይሄንን በመላው ዓለም ዘንድ ትኩረት እያጣ የሚገኘውን ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ የመጣውን በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን እጅግ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና አፈና እንዲቆም እርዳታ ለጋሽ አገሮች፡ አህጉራዊ እና ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች በኢህአዴግ መንግስት ላይ ግፊት በማድረግ በቃሊቲ፡ በቂሊንቶ፡ ዝዋይ እና ሌሎችም እስርቤቶች የሚገኙ ጋዜጠኞች፡የተቃዋሚ ፖርቲዎች መሪዎች እና በሺህ የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች እንዲፈቱ ለማሰብ መጽሀፋቸውን በዝግጅቱ ላይ ይፋ ለማድረግ መወሰናቸውን ገልጸዋል።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር በህይወት ከተለዩ በኋላ በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና አፈና ይሻሻላል ሲባል ጭርሱን ተባብሶ መቀጠሉን በመጠቆም በቅርቡ ከማርቲን እና ዩዋን ጋር በተመሳሳይ ወራት እና ወንጀል ታስራ አሁንም በቃሊቲ እስርቤት ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባት ያለችውን ርዕዮት ዓለሙን እንደዓብነት አንስተዋል።
ርዕዮት በእስር ላይ በምትገኝበት በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እየተፈጸመባት ያለውን ኢሰብዓዊና ኢህጋዊ በደሎች ለመቃወም ከመስከረም ፩ ጀምሮ በረሃብ አድማ ላይ መሆኗን በመጠቆም ይህ በገዥው ስርዓት ሎሌዎች በህሊና እስረኞች ላይ የሚካሄደው በደል እና ግፍ ቅጥ እያጣ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ውብሸት ታዬ ከእስር እንዲፈታ ያቀረበው የይቅርታ ደብዳቤ በገዥው መንግስት ተቀባይነት ካለማገኝቱም ባሻገር ከአራት ወራት በፊት ከቂሊንጦ ወደ ዝዋይ እስርቤት ሆን ተብሎ በመዛወሩ ልጁ እንዲሁም እድሜያቸው ከሰማኒያ ዓመት በላይ የሆናቸው ወላጆቹ ተመላልሰው ሊጠይቁት እንዳልቻሉ ተገልጿል።
ኤቢፍ የተባለው የስዊድን የሲቪክ ተቋም፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ድንበርየለሹ የጋዜጠኞች ማህበር በስዊድን መስከረም 4፣ 2006 ዓም የተካሄደውን ዝግጅት በጋራ በመሆን ማዘጋጀታቸውን ቴዎድሮስ አረጋ ከስቶክሆልም ዘግቧል።
በሌላ ዜና ደግሞ መንግስት በስዊድን ስቶክሆልም ያዘጋጀው የቦንድ ሽያጭ መርሀግብር በተቃውሞ እንዲጨናገፍ ተድርጓል።
በኢትዮ ስዊድን መርሃግብር አስተባባሪነት ከጎትምበርግና ስቶክሆልም የተሰባሰበዉ የተቀዋሚ ኃይል የአዳራሹን መግቢያ በሰዉ በመዝጋትና የራሳቸዉን ቀስቃሽ ሙዚቃዎችን በማጫወት የአዳራሹን መግቢያና አካባቢዉን ተቆጣጥረዉት ስለነበር ይህን ጥሶ የሚገባ ባለመኖሩ አዳራሹ ከቦንድ አዘጋጆች በቀር ባዶዉን እንዲዉል መደረጉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በምሽቱ የሙዚቃ ፕሮግራም ላይ በተፈጠረ ረብሻም የሙዚቃ ዝግጅቱ እንደተጠበቀው አለመካሄዱን መረጃው አመልክቷል። በስዊድን መንግስት ያዘጋጀው የቦንድ ሽያጭ ሲከሽፍ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

Tuesday, September 10, 2013

የጠ/ሚ ባለቤት በቤተመንግስት ኑሮ መሰላቸታቸውን ገለጹ

ኢሳት ዜና :-ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ የቤተመንግስት ኑሮ የሚመች አለመሆኑንና የቀድሞ ጠ/ሚኒስትርንም አኗኗር በማየት ያዝኑ እንደነበር ተናግረዋል።
roman-tesfaye-first-lady-of-ethiopiaቀዳማዊት እመቤቷ ትላንት ከወጣው መንግስታዊው ዘመን መጽሔት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የቤተመንግስት ሕይወት አስደሳች አይደለም ብለዋል፡፡ “ የቤተመንግስትን ሕይወት ለማንም ተመኝቼው አላውቅም፡፡ የሴቶች ጉዳይን ስናቋቁም ስምንት ወር ተመላልሼበታለሁ፡፡ ዛሬ እናንተ ተፈትሻችሁ እንደገባችሁት እኛም ተፈትሸን ነበር የምንገባው፡፡ እዚህ ግቢ ስገባ ወደጠ/ሚኒስትሩ ቤተሰቦች መኖሪያ ማዶ እያየሁ አዝንላቸው ነበር፤ግን ለሰው አላወራም፡፡ እዚህ ግቢ ውስጥ የሚኖር ሰው እንዴት ተበድሎአል እያልኩ እገረም ነበር፡፡ እና እኔን ኑሪ ቢሉኝ የማላደርገው መስሎ ይሰማኝ ነበር፡፡    ብለዋል፡፡
አስተዳደጌ ያስተማረኝ ከሌሎች ጋር በጋራ መኖርን ነው ያሉት ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ራስን ለማዝናናት፣ዞር ብሎ ቡና ለመጠጣት ፣ዘመድ ጓደኛ እንደልብ ለማግኘት አስቸጋሪ መሆኑን በመጥቀስ ከዚህ አንጻር  የቤተመንግስት ሕይወት ነጻነት የለውም ሲሉ አስረድተዋል፡፡
“ለአንዳንዶች የቤተመንግስት ሕይወት የተንደላቀቀ መስሎ ይሰማቸዋል” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄም በአጭሩ እንደሚታሰበው ዓይነት አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የቀድሞ ኑሮአቸው ከአሁኑ በምን ይለይ እንደሆነ ተጠይቀውም የምግብ ማብሰያውና የአዘገጃጀቱ ሁኔታ ለየት እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡ “ቤተመንግስት የበሰለው ነገር በንጽሕና የሚቀርብበት ነው፡፡ አዘጋጆቹ በዘርፉ ሙያው ያላቸው ናቸው፡፡ ብዙ ዓመት ያገለገሉ ወጥ ቤቶች አሉ፡፡ ከዚህ ውጪ እንግዲህ ጥበቃው አለ፤ይህው ነው” በማለት አስረድተዋል፡፡
ወ/ሮ ሮማን ከጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አብራክ የወለዱዋቸው የ23፣የ20 እና የ18 ዓመት ሶስት ሴት ልጆች እንዳሉዋቸውም በቃለምልልሳቸው ተናግረዋል፡፡
ባለቤታቸው አቶ ኃይለማርያም በአመራራቸው አስቸጋሪ ሁኔታ ያጋጥማቸው እንደሆን ተጠይቀውም ሲመልሱ አስቸጋሪ ነገር እንኩዋንስ አገር የሚያክል ነገር በመምራት ላይ ቀርቶ ታችም ሞልቱዋል፡፡ “አሁን ያለንበት የግሎባላይዜሽን ዘመን ነው፡፡ ብዙ ዓለምአቀፋዊ ይዘት ያላቸው ጠቃሚም ጎጂም ነገሮች አሉ፡፡ የኢትዮጽያ ሕዝብ አሁን ለመብቱ መታገል ተለማምዶአል፤ መጠየቅን ለምዶአል፡፡  ፈጣን ዕድገትን ይፈልጋል፡፡ ሠላምን፣ ተረጋግቶ መኖርን ይፈልጋል፡፡ መልካም አስተዳደርን ይፈልጋል፤ መልካም አስተዳዳር ሲባል ደግሞ በውስጡ ብዙ ጉዳዮች አሉት፡፡ እና ይህን ሁሉ ፍላጎት ይዞ ሕዝብን የሚያረካ አመራር መስጠት እያደገ የሚሄድ ነው” ብለዋል፡፡
ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ከቀድሞዋ እመቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቤተመንግስቱን ተረክበው ከባለቤታቸውና ልጆቻቸው ጋር የቤተመንግስት ኑሮ ከጀመሩ ገና አንድ ዓመት አልደፈኑም፡፡
ወ/ሮ ሮማን የቤተ-መንግስት ኑሮ ነጻነት እንዳይኖረው የተደረገበትን ምክንያት አላብራሩም፣ ነጻነት እንዲኖረው ለማድረግም ምን ምን እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው አልዘረዘሩም። ወ/ሮ ሮማን  ህዝቡ ስለመብቱ መታገል ተለማምዷል በማለት መናገራቸው በቅርቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች ካደረጉት ሰልፍ ጋር ይያያዝ አይያያዝ ወይም፣ ይህ ልምምድ ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ ፣ በአቶ ሀይለማርያም የስልጣን ጊዜ የመጣ ክስተት መሆኑንና አለመሆኑን አላብራሩም።

Monday, September 9, 2013

“በስልጣን ምክንያት ህወሓት ለሁለት የተከፈለ ይመስለኛል” – አቶ ገብሩ አስራት (ቃለ ምልልስ)

ሐገር ቤት የሚታተመው ሎሚ መጽሔት አቶ ገብሩ አስራትን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አነጋግሯቸዋል። ዘ-ሐበሻ ለአንባቢዎቿ ይጠቅማል በሚል እንደወረደ አቅርባዋለች።
ሎሚ፡- ባለፈው መቀሌ ላይ “አረና” ሕዝባዊ ስብሰባ አከናውኖ ነበር፡፡ የነበረው ሁኔታ በአጠቃላይ ምን ይመስል ነበር;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ የመቀሌውን ስብሰባ ከሁለት ጉዳዮች አንፃር ልንመለከተው እንችላለን፡፡ አንዱ ሕዝቡ እንዴት እንደተቀበለው ስብሰባውን … ሁለተኛው መንግስት ወይም በክልሉ ያለው ፓርቲ ስብሰባው እንዳይካሄድ ያደረጉትን ጫና በተመለከተ መመልከት ይቻላል፡፡ እንግዲህ አስቀድሜም መንግስት ስብሰባው እንዳይካሄድ የፈጠረውን ጫና ነው የማየው፡፡ እንግዲህ ትግራይ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ህወሓት ነው፡፡ ህወሓት ከእሱ ውጭ ሌላ ፓርቲ እዛ ቦታ ላይ እንዲንቀሳቀስ ፍላጐት የለውም፡፡ ይህም ባፈለው 2002 ዓ.ም. በተካሄው ምርጫ ጠ/ሚ መለስ ትግራይ ውስጥ ምንም አይነት ክፍተት መኖር የለበትም፣ ምንም አይነት የሀሣብ ልዩነት መኖር የለበትም ብለው የተናገሩበትና በርካታ ስድቦች የተሰነዘረበት በተለይም በ”አረና” ላይ በርካታ ስድቦችን ያወረዱበት ጊዜ ነበር፡፡ እንግዲህ አሁን ያለው አመራርም የእሣቸውን “ሌጋሲ” ፈለግ እከተላለሁ የሚል ስለሆነ አካሄዱ ተመሳሳይ ነው፡፡ በትግራይ ውስጥ ምንም አይነት የፖለቲካ አስተሳሰብ እንዲኖር አይፈልግም፡፡ በህገ መንግስትም ፣ በቃልም ተቃዋሚ ቢኖር አንጠላም ሊሉ ይችላሉ፡፡ ዋናው ስጋታቸው በአካባቢው የተለየ ሀሣብ ፣የተለየ አመለካከት ፣ የተለየ አደረጃጀት እንዳይኖር ስጋትና ጭንቀት ያለባቸው ስለሆነ አጠቃላይ ድርጅቱን በእነሱ ስር የተደራጀ ሲቪክ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ድርጅቶችን አደራጅተው ነው አንድ ፓርቲ በዛ አካባቢ ስብሰባ እንዳያካሂድ የሚያደርጉት፡፡ ባለፈው ጊዜም ስብሰባ ስናካሂድ እንደውም እነሱ በሚመሯቸው ድርጅቶች ፣ ኩባንያዎች /ኢፈርት/ ሠራተኞችን ሰብስበው በዚህ ስብሰባ ላይ መገኘት ከጠላት ጋር እንደማበር ይታሰባል ብለዋቸዋል፡፡ እና ስለዚህ ስራ ለማግኘት አትችሉም፣ ስጋት ላይ ትወድቃላችሁ ፣ ከጠላት ጋር የመተባበር ያህል አድርገን ነው የምናየው ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡
ይህንን ካሉ በኋላም በዚህም አላበቃም በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ መሠረት እንደተፈቀደው ማንም ፓርቲ ሊቀሰቅስ ይችላል፡፡ መቀስቀስ የማይችለው በትምህርት ቤትና በቤተ እምነት ቦታ ውስጥ እንጂ በሌላ ቦታ ድምፅ ማጉያ ተጠቅሞ መቀስቀስ ይችላል የሚል ነገር አለ፡፡ መቀሌ ላይ ግን ሌላ ህግ አውጥተዋል ወይም አውጥተናል ነው የሚሉት፡፡ እኛ ግን አላየነውም፣ ህጉ ምንድነው የሚለው ማንኛውም እንቅስቃሴን ማጉያ ተጠቅሞ መቀስቀስ አይቻልም ነው የሚሉት፡፡ ይሄ እንግዲህ ከሀገሪቱ ህግ ፣ ከፌዴራል ህግ ጋር የሚጣረዝ ህግ ነው፡፡ ህግም ቢሆን ማለቴ ነው፡፡ ማውጣትም አይችሉም፡፡ እንደዚህ ያለ የምርጫ ቦርድ ሕግ እያለ መንግስት ወይም አስተዳደር ይሄንን ህግ ሊያወጣ አይችል፡፡ እኛ ህግ አውጥተናልና መንቀሣቀስ አትችሉም እያሉ ነው የሚናገሩት፡፡ ለምን ስንላቸው ደግሞ ድምፅ ማጉያው ማለት ነፍሰ ጡሮችንና በሽተኞችን ሊያውክ ስለሚችል መናገር አይቻልም ፡፡ በዛ ምክንያት ነው የከለከል ነው ይላሉ፡፡ ያም ሆኖ ግን መስኪዶች፣ ቤተክርስቲያኖች በድምፅ ማጉያ መልእክት ያስተላልፋሉ፡፡ ራሣቸው ህውሓቶችም በድምፅ ማጉያ ዳንኪራ እየመቱ የሚያጥለቀልቁበት ሁኔታ አለ፡፡ ለተቃዋሚዎች ነው ያልተፈቀደው እንጂ ራሣቸው በማይክራፎን ከተማውን የሚያውክ ነገር ይጠቀማሉ፡፡ ስለዚህ በዚህ ምክንያት ያንን ከለከሉን፡፡ እና ይሄ ህግ ይፈቅድልናል ብለው የኛ አባላትም ተንቀሣቀሱ፡፡ ግን አሰሯቸው፡፡ ሁለት ሦስት ጊዜም ነው ይህንን ያደረጉት፡፡ ሹፌሮችንና የተከራየነውንም መኪና አገቱ፡፡ ስለዚህ በዚህ መልኩ ስብሰባ እንዳይካሄድ አግተዋል፡፡ በንጋታው ደግሞ ስብሰባ ስናካሂድ እያንዳንዱ የቀበሌ አስተዳደር ማን እንደሚገባ እንዲመለከት እዛ አሰልፈዋቸው ነበር፡፡ አብዛኞቹም ሴቶች ናቸው፡፡ /የቀበሌ ሴቶች/ እነዚህን አሠልፈው ማነው ወደዚህ ስብሰባ የሚገባው የሚል ሊስት ይዘው አስቀመጡ፡፡
ጭራሽ ስብሰባ እንዳይካሄድ ነው የሞከሩት፡፡ በሌላም እያንደንዱ ቀበሌ ለሕዝቡ ስብስባ እንዲመጣ በፅሁፍ ጭምር ደርሰው እንድትገኙ የሚል አስተላለፉ ….የምንናገረው ስለመልካም አስተዳደር ፣ ስለ ንግድ ምናምን ነው ብለው መቅረታ የለባችሁም ወሣኝ ስብሰባ ነው ብለው ፣ እኛ ስብሰባ በምናደርግበት ቀን እነሱም ስብሰባ ጠሩ፡፡ ይሄ አካሄድ ደግሞ ምንም አይነት ሰው ወደኛ እንዳይመጣ የማድረግ አላማ ያለው ነው፡፡ ያም ሆኖ ግን ሕዝቡ ፍላጐት ነበረው እንዲያውም ስብሰባውን እንድናካሂድ ግፊቱ የመጣው ከሕዝቡ ነበር፡፡ ያም ሆኖ እነሱ ባይከለክሉት ኖሮ አዳራሹም አይችልም ቦታም አይበቃም ነበር፡፡ ይሄም ሆኖ ወጣቱ ይሄን ሰብሮና ጥሶ አድራሹን ሞልቶታል፡፡ እና እዚህ ላይ ለማለት የምፈልገው በተለይ በሁለት ጉዳዮች ላይ እኛ ያቀረብነው በከተማ የሊዝ አዋጆች ላይ ፣ በነጋዴዎች የግብር ጫና፣ በዜጐች ሰብአዊ መብት እጦት እንደዚህ እንደዚህ ያሉ በርካታ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡ ሕዝቡ ግን ትኩረት አድርጐ ያቀረበው ነፃነቱን እንደተነፈገ ነው፡፡ ትግራይም ውስጥ እንደተነፈጉ ተናጋሪዎች ናቸው፡፡ እኛ ንግግሩን ጀመርነው እንጂ የጨረሰው እዛ የተሰበሰበው ሕዝብ ነው፡፡
ሌላው ደግሞ ይሄ የሊዝ መሬት ዜጐችን ጭሰኛ ለማድረግ እየሞከረ እንዳለ በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡ መሬታችንን ቀሙን፣ በወላጆቻቸው /ውርስ/ ያገኙት መሬት ላይ ዋስትና እንዳጡ ፣ ይህንንም ተናገሩ፡፡ እንግዲህ የሚገርመው ስብሰባውን በፀሎት ለመጀመር ነው ፕሮግራም የያዝነው፡፡ ሁሉም የስብሰባው ታዳሚ ተነስቶ ለሰማእታት ፀሎት ሲያደርግ አንድ ወጣት ግን ከመቀመጫው ሣይነሳ ቁጭ ብሏል፡፡ ኋላ ላይ ግን ለምን በፀሎቱ ወቅት እንደተቀመጠ ምክንያቱን ተናገረ፡፡ ይሄ ወጣት ሲናገር “እኔ እናንተ ለምን ተነስታችሁ እንደምትፀልዩ አልገባኝም፡፡ ምክንያቱም እኔ አባቴ በትግሉ ተሰውቷል፣ ወንድሜና እህቴ ተሰውተዋል፡፡ ግን ያመጡልን ምንም ነገር የለም፡፡ ለምንድነው የምፀልየው; እኔ የምፀልየው ኢትዮጵያው ውስጥ ነፃነት ሲረጋገጥ፣ መብት ሲረጋገጥ ነው እንጂ አሁን ቆሜ አልፀልይም፡፡ ቤተሰቦቼ የተሰዉበት ሁሉ ተግባራዊ እየሆነ አይደለም፡፡ አፈና ፣ ሙስና ይህንን ለማምጣት ከሆነ የተሰዉት አልፀልይም፡፡ የምፀልየው ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነት ሲረጋገጥ ብቻ ነው” ብሏል፡፡ ይህ ንግግር ተሰብሳቢውን በጣም ያስገረመ ንግግር ነው የነበረው፡፡በአጠቃላይ መንግስትና የክልል ፓርቲ ስብሰባ እንዳይካሄድ ሕዝቡ ሌላ አማራጭ እንዳይሰማ ቢያደርጉም ሕዝቡ ግን ከፍተኛ ፍላጐት ነበረው፡፡ እንዲያውም እኛ ካሰብነው ጊዜ በላይ ተወያይቶ በጥሩ ሁኔታ ስብሰባውን አጠናቀናል፡፡
ሎሚ፡- አንዳንድን ዘገባዎች አሉ ይህ በሕዝብ ውስጥ የሚባለው ነው መረጃውን በእርስዎ አንደበት የማስተላለፉ መልእክት ደግሞ የእርስዎ ይሆናል፡፡ አረና ጥሩ እየተንቀሣቀሰ ቢሆንም የአባላቶቹ ወደ አሜሪካ መጓዝ በፓርቲው ላይ ችግር አይኖረውም ወይ የአቶ ስዬ እና የአቶ አሰግድን የሚያነሱ ሰዎች አሉ;
አቶ ገብሩ፡- ይሄ ምናልባትም የመረጃ ጉዳይ እንዳይሆን ለመናገር እሞክራለሁ፡፡ አቶ ስዬ የአረና አባል አይደሉም፡፡ የአንድነት አባል ናቸው፡፡ አቶ አስግድም ተመልሰዋል፡፡ አሁን ትግራይ ውስጥ ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ የእኛ አባል ሆኖ ከሀገር ውጭ የሚገኝ የለም፡፡ ስለዚህ ይህን መረጃ ሕዝብ እንዲያውቀው ይገባል፡፡
ሎሚ፡- በህወሓት ውስጥ እውነት ልዩነት አለ; ህወሓት ለሁት ተከፍሏል የሚባል ነገር አለ ይሄን እንዴት ይገልፁታል;
አቶ ገብሩ፡- እኔ እንግዲህ በፖለቲካ ምክንያት ፣ በፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ህወሓት ውስጥ መከፋፈል አልተመለከትኩም፡፡ ያም ሆኖ በስልጣን ምክንያት ህወሓት የተከፈለ ይመስላል፡፡ ይህም የታየው መቼ ነው ባለፈው የፓርቲው ጉባኤ በተካሄደበት ጊዜ ነባሮቹን ሙሉበሙሉ ጠራርጐ አስወጥቷል፡፡ ካድሬዎቹ ይሄ የሆነው ምንድነው ህወሓት ውስጥ የተጠናከረው በካድሬ ደረጃ አባል ነው ስልጣኑን የተቆጣጠረው እንጂ ራሱ ሀሣብ ሊያመነጭ የሚችል ፣ ሀሣብን ሊቀምር የሚችል፣ ንድፈ ሀሣብን በደንብ ተገንዝቦ ሊያስረዳ የሚችል ኃይል ህወሓት ውስጥ አሁን የለም፡፡ ከፋም በጀም የተሻለ አቅም ያላቸው ሰዎች ከዚህ ተገለዋል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡ ስለዚህ የስልጣን ሽግሽግ ነው ለዚህ ያነሱት፡፡ ይህንን መሠረት አድርገው ነባር የተባሉትን ጠራርገው አስወጡ፡፡ እዚህ ላይ ግን ነባር የተባሉትንና ተጠርገው ከወጡት እኩል በፓርቲው ረጅም እድሜ ያላቸው ደግሞ እዛው ቀርተዋል፡፡ ስለዚህ ነገሩ የስልጣን ሽኩቻ ይመስላል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡
ሎሚ፡- አሁን የኃይል ሚዛኑ የትኛው ክፍል ጋር ነው;
አቶ ገብሩ፡- ይሄ ኢትዮጵያ ውስጥ በጣም አስቸጋሪ ነገር ነው፡፡ እንግዲህ የኢትዮጵያ ፖለቲካና ስልጣን የተመሠረተው በማን ላይ ነው የሚለውን መመልከቱ ጥሩ ነው፡፡ ሦስት አካሎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለት የመንግስት አካላት፣ ሦስተኛው መከላከያና የደህንነት አካላትን ነው ማየት የሚቻለው፡፡ አቶ መለስ በነበሩበት ጊዜ እነዚህ ሦስት አካላትን ተቆጣጥረው የሄዱበት ጊዜ ነበር፡፡ እንግዲህ የአቶ መለስ መንግስት አምባገነን መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ እንደ አምባገነንነቱም ሁሉንም የስልጣን አካላት ተቆጣጥረው በእጃቸው ውስጥ አስገብተው ቆይተዋል፡፡ እንደውም አሁን ኢህአዴግ ተዳክሟል የሚያሰኘው ምንድን ነው በአንድ ሰው ተሰባስቦ ፣ የአንድ ሰው ፈላጭ ቆራጭ፣ ስልጣን የነበረው አሁን ተበታትኗል፡፡ ከስልት አንፃር ይሄ መዳከምን ያሣያል፡፡ ይህ ከሆነ በኋላ ስልጣኑ የት ላይ ነው የሚለው ነገር በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ እንደ አቶ መለስ ተጠናክሮ የወጣ ሰው የለም፡፡ የአቶ መለስ ፍላጐት ቀድሞም ምንድነው የፑቲን አይነት አስተዳደር ነው በዚህች ሀገር ላይ ፍላጐታቸው የነበረው፡፡ ደካማውን ፊት ላይ አስቀምጠው እሣቸው ከኋላ ሊነዱት ነበር አቶ ኃ/ማርያምንና ሌሎችንም ወደ ስልጣን ያመጡት፡፡
ያም ሆኖ ግን እሣቸው አልቆዩም፡፡ አቶ ኃ/ማርያም በዚህ አጋጣሚ ስልጣን ያዙ፡፡ አሁን አቶ ኃ/ማርያም መከላከያውንና ደህንነቱን በእጃቸው ለመቆጣጠር ይችላሉ 1111 የሞራል ብቃትስ አላቸወይ; የፖለቲካው ብቃትስ አላቸወይ; የሚለው ጥያቄ የሚያስነሳ ነገር ነው፡፡ ፓርቲውንስ ቢሆን እንግዲህ ነባሮች ዳግም ተመልሰዋል ብአዴን ውስጥ አቶ መለስ እያሉ ውጡ ተብለው ታዘው ወጥተው የነበሩትም እንደገና ተመልሰው መጥተዋል፡፡ እነዚህንስ ለማዘዝ ይችላሉ ወይ;ከፍተኛ ውሣኔዎች ላይ የማዘዝ አቅም ይኖራቸዋል ወይ; የሚለው አንድ ጥያቄ ነው፡፡ እንግዲህ በመንግስት የሚባሉት ፣ በፓርላማ፣ በካቤኔ ውስጥ የዚህ ነፀብራቅ ነው፡፡በደህንነቱ፣ በመከላከያው የማዘዝ ስልጣን ከሌለህ በመንግስት ውስጥም የማዘዝ ችሎታህ አነስተኛ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አሁን ችግሩ የስልጣን ክምችት በአንድ አካል ላይ አለ፡፡ ይሄ ነው የሚወሰነው፡፡ ደህንነቱም ሆነ መከላከያው ትልቅ ተፅእኖ አለው በኢትዮጵያ፡፡ እንደውም ወሳኙ እሱ ነው፡፡ እሱን ማዘዝ፣ ማሰማራት ፣ እሱን መቆጣጠር የማይችል ኃይል በኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይል ይዣለሁ ማለት አይችልም፡፡ ይህንንስ ማድረግ ይችላል ወይ; አሁን ያለው አመራር ለሚለው ነገር ጥያቄ ውስጥ ያስገባል፡፡ ፓርቲዎችም ቢሆን ከአቶ መለስ ሞት በኋላ የየራሣቸው ነፃነትና መብት ለማስከበር አዝማሚያም እየታየባቸው ነው፡፡ የብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ህወሓት በአጠቃላይ የፖለቲካ ሂደት ላይ ተፅእኖ ለማሣደር እየሞከሩ ነው ያሉት፡፡ በይፋ ያልወጣ ሽኩቻ እየታየ ነው፡፡ ውስጥ ለውስጥ፡፡ ድሮ የነበረው የአንድ ግለሰብ ተፅእኖ አሁን የመሰበር ሁኔታዎች ነው ያሉት፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉንም ለመወሰን ኃይሉም አቅሙም ያለው የለም፡፡ የሚፈለገው እሱ ነው ወይ ሌላ ጥያቄ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሄ የአቶ መለስ ሌጋሲ የሚባለው ግን እንደዛ ያለ ሰው ካልፈጠረ በስተቀር ጥንካሬ አለው ብሎ ለማለት አይቻልም፡፡
ሎሚ፡- አሁን እንግዲህ በስርአቱ ውስጥ ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ መንሰራፋቱ ይነገራል፣ የሚታይም ነገር ነው፡፡ከሀገር ውጭም ገንዘብ የማሸሽ ሁኔታ አለ ይሄን እንዴት ይመለከቱታል;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ ሁልጊዜም እንደምለው ራሱ የሙስና ምንጭ በኢትዮጵያ ያለው የሙስና ምንጭ የለሚው ነገር ካልታወቀ መፍትሄም አይገኝለትም፡፡ ኢህአዴግ ሙስናን እየታገልኩ ብሎ ለማስመሰል የተወሰኑ ባለስልጣኖችንና ነጋዴዎችን ያስራል፡፡ ይፈታል፡፡ ግን ይሄ መፍትሄ ነው ወይ; በኢትዮጵያ የሙስና ምንጭ መሠረት የሆነው እነዚህ ነጋዴዎች ናቸው ወይ; የተወሰኑ ባለስልጣናት ናቸው ወይ; የሚለውን ነገር ማንሣቱ የሚጠቅም ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሙስና ሊቀንስ፣ ሊቃለል የሚችለው ከስርአቱ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት አለው፡፡ የአንድ ስርአት ፓርቲ አገዛዝ ከሆነ ዞሮ ዞሮ ሙስናን ነው የሚያነግሰው፡፡ደጋፊዎቹን ያጠናክራል፣ በሀብት ያጠናክራል፣ በገንዘብ ያጠናክራል፣ ፖሊሲው ነው፡፡ አባሎቼ የሚላቸውን ቢሰርቅ ፣ ቢዘርፍ ምንም ሊላቸው አይችልም፡፡ ፖለቲካውን የሚቃወሙ ሊነካኩ የሚችሉ ሰዎች አንዳንድ ጊዜም በሰውም ምንም ለውጥ አያመጣም ብሎ የሚያስባቸውን ሰዎች በሙስና ይቀጣል እንጂ ከመሠረቱ ስርአቱ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ይሄ በውጭ ሀገር ገንዘብ አላቸው ወይ; አስቀምጠዋል ወይ; የሚለው ነገር በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን የአለም ተቋማት እንደሚነገረው የሸሸው ገንዘብ በርካታ ነው፡፡ ይሄ ገንዘብ የማነው የኔ ነው የሚል ባይታወቅም በኢትዮጵያ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየሸሸ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ግን ወደዛ መሄድ አያስፈልግም፡፡ እዚህ ሀገር ያለው ሀብት ከየት መጣ የሚለው ነገር ቢጠየቅ እኮ መልስ የለም፡፡ሰርቶ ነው ወይ; ከደሞዙ ነው; በተለይ አንድ የመንግስት ባለስልጣን ትላልቅ ቤቶችን የሚያሰራ ደሞዝ አለው ወይ; ህንፃዎችን የሚያሰራ ደሞዝ አለው ወይ; ብዙ ሀብት ቤተሰቦቹን በከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውጭ ድረስ ልኮ የሚያስተምር ደሞዝ አለው ወይ ተብለው ቢጠየቁ የኢህአዴግ አመራሮች መልስ የላቸውም፡፡ ስለዚህ ሙስናው የራሱ የስርአቱ ባህሪ ነው፡፡ ምክንያቱም ሙስናን እንታገል ቢባል፣ ኢህአዴግ በሚከተለው አግባብ እንዴት ሙስናን መታገል ይቻላል; ነፃ ማህበረሰብ ፣ ሲቪል ማህበረሰብ በሌለበት እኮ ይሄ ሙሳኝ አለ ብሎ መቃወም አይቻልም፡፡ ጠንካራ ነፃ ጋዜጦች “Invest get journalism”መስራት በማይቻልበት ሁኔታ እንዴት ነው ሙስናን መዋጋት የሚቻለው; የመንግስት ተጠያቂነት ግልፅነት በሌለበት እንዴትነው ሙስናን መታገል የሚቻለው; ሕዝብ ሰልፍ ወጥቶ መቃወም በማይችልበት፣ ተሰብስቦ መነጋገር በማይችልበት እንዴት ነው ሙስናን መታገል የሚቻለው; ስርአቱ በባህሪው አምባገነናዊ ስርአት ነው፡፡ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ብሎ የአንድ ፓርቲ ፈላጭ ቆራጭነት አረጋግጣለሁ የሚል መንግስት ከሙስና አይነፃም፡፡ ነፃ ሊሆን አይችልም፡፡ በአለምም ያየነው፣ በአፍሪካም የሚታየው ፓርቲዎች የህብረተሰቡን እንቅስቃስቃሴ በሙሉ “ገዢ ፓርቲዎች” ሕዝቡ ትንፍሽ እንዳይል ፣ እንዳያጋልጥ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ኢህአዴግም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ መታየት ያለበት የአንድና ሁለት ባለስልጣን የማሰርና የማጋለጥ ጉዳይ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር ስርአቱ በቁርጠኝነት መታገል የሚችል እስከሆነ ብቻ ነው፡፡ ይሄንን ደግሞ ኢህአዴግ አይችልም ያውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ መሬት እንደተዘረፈ ያውቃል፡፡ እሱ ነው የሚያዘርፈው፡፡ የመንግስት በጀት እንደተዘረፍ ያወቃል ግን እራሱ ነው የሚያዘርፈው፣ የመንግስት ልማት ተቋማት በሚሊዮኖች ይዘረፋሉ ያውቃል መንግስት ግን መፍትሄ የለውም፡፡ መፍትሄም ከኢህአዴግ ይመጣል ብሎ ማሰብ የዋህነት ይሆናል፡፡ ምንም ሊመጣ አይችልም፡፡
ለዚህም ነው ከአመት አመት እየተባባሰ እንደውም አሁን የስርአቱ ዋና መገለጫ እየሆነ ያለው ከዚህ በመነሣት ነውና፡፡ አንድ እንደ አቅጣጫ መታየት ያለበት፣ መረሳት የሌለበት ሙስና ከስርአቱ የሚመነጭ ስለሆነ ፣ በፀረ ሙስና በኩል የተወሰኑትን በማሰር የሚቋጭ አይደለም፡፡ሰፊ ነፃነት፣ሰፊ መብት፣ ጠንካራ የህግ የበላይነት፣ ነፃ ባለስልጣኖችን ሊጠይቅ ሊያስር የሚችል አቃቢ ህግ “ነፃነት ያለው” ፍርድ ቤት ሊወስንባቸው የሚችል ያለምንም ተፅእኖ ከሌለ ሙስናን መታገል እንዴት ይቻላል፡፡ ስለዚህ ታዩታላችሁ ሙስና ኢህአዴግ እስካለ ድረስ እየባሰበት የሚሄድ ይሆናል፡፡ አሁን ተራ ሙስና አይደለም የማፍያ አይነት የተደራጀ ሙስና ነው እየተካሄድ ያለው፡፡
ሎሚ፡- እንደታዘቡት ከሆነ ፣የሙስሊሙ ጥያቄ አለ ይሄን እንዴት ይመለከቱታል; ሌላው ከቅርብ ቀናት ወዲህ በመንግስት በኩል አክራሪነት ፣ ሽብርተኝነት፣ አሸባሪነት የሚሉ ቃላት ይሰማል ይሄስ በእርስዎ እይታ እንዴት ታዘቡት;
አቶ ገብሩ፡- እንግዲህ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጊዜ ተናግረናል፡፡ እኔ እንግዲህ ኢህአዴግ አንዳንድ ችግሮች ሲነሱ የሚሄድበት አግባብ ችግሮች አሉበት፡፡ የሙስሊሙ ጥያቄ ፣ የአባይ ጥያቄ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ እነዚህ በዚህ አገር ከባድ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ በተለይ በሙስሊሞች ጉዳይ መታየት ያለበት ካለው ማህበረሰባዊ እድገት፣ አለም አቀፋዊ ሁኔታ መንገድ ነው መታየት ያለበት፡፡እንግዲህ የሙስሊሞች ጥያቄ መታየት የጀመረው እኮ መለስ በነበረበት ጊዜ ነው፡፡ እንደማስታውሰው እኔ ከተለያዩ የአለም ክፍሎች የተውጣጡ ፣ የሙስሊም አባላት መጥተው ከአቶ መለስ ጋር ተገናኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሙስሊሞች አያያዝ የሚያሳስባቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ጥያቄዎችም ያኔ አንስተዋል፡፡ ካነሷቸው ጥያቄዎች መሀል፣ የበአላት ማክበር፣ ወለድ የሌለው ባንክ የመክፈት ጉዳይ እንዲህ እንዲህ ያሉ ወደ አስር የሚጠጉ ጥያቄዎች አንስተው ነበር፡፡ በወቅቱ እናየዋለን የሚል መልስ ነው የተሰጣቸው፡፡ ከዛ በኋላ የታየም ነገር የለም፡፡ ውስጥ ለውስጥ የሚነሱ ጉዳዮች አሉ፡፡ ብዙ የመብት ጥያቄዎች፡፡ ይሄ እያለ ግን ኢህአዴግ ይሄን የሚያባብስ እርምጃ ወስዷል፡፡ ምንድነው እንደምታስታውሰው በተለይ “ፌድራል ጉዳዮች” የሚባል የመንግስት አካል የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን በሌላ ሙስሊም ለማስጠመቅ ሙከራ አደረገ፡፡ “አልሀበሽ” የሚባል ገንዘብ አውጥቶ ይሄን ተማሩት አለ፡፡ እያንዳንዱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስሊም በዚህ ውስጥ እንዲጠመቅ ሙከራ አደረገ፡፡ ሙስሊሞች ተቃወሙት ፣ ሃረር ላይ ….. ሚኒስትሩ ሣይቀር ስብሰባ አደረገ፡፡ ይሄ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ …. አንድን ኃይማኖት በሌላ ኃይማኖት በዚህ እመን ማለት ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ያለጥርጥር ነገሩ ከዚህ ተነሣ ከዛ የአወሊያ ትምህርት ቤትም ተነሣ ይሄ የቆየ ነው፡፡ ድሮ የነበረ ትምህርት ቤት ነው፡፡ ያንን ለመቆጣጠር ሞከረ፣ ያም አይሆንም የሚል ምላሽ ቀረበ፡፡
እንደገና የምርጫ ጉዳይ ተነሣ፡፡ ቀላል ጥያቄ በጣም ቀላል …. ምርጫው በመስኪዶች ይሁን የሚል፡፡ ይሄ ሁሉ ኢህአዴግ የማያዝበት መንገድ ግን ሽንፈት ነው የሚመስለው፡፡ አንዳንዶቹን ጥያቄዎች መመለስ ሽንፈት ስለሚመስለው ነገሩን ያጦዘዋል፡፡ ወደ አስቸጋሪ ሁኔታ ይገፋዋል፡፡ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች እንደማውቃቸው በመሠረቱ በጣም ተቻችለው በመኖር ተግባብተው በመኖር የሚታወቁ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ የሱፊ እምነት ፣ ካተሚያ እምነት በኢትዮጵያ ያለው ተቻችሎ የኖረና የሚኖር ሙስሊም ነው፡፡ ያም ሆኖ ግን ልክ በክርስቲያኑ ውስጥ እንደሚታየው ድሮ የሚታወቁት ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ አልፎ አልፎ የድሮ ፕሮቴስታንቶች ይታወቁ ነበር፡፡ በኋላ ላይ ግን ጴንጤዎች መጡ፣ ሌሎችም መጡ፣ ጆባ መጣ ይሄ በነበረው አይን ሲታይ ፅንፈኛ ነው እና ክርስቲያኑ ሁሉ ያኔ ተደናገጠ ግን ሊያቆመው አይችልም፡፡ ከአለም ጋር ይገናኛል፡፡ ሕዝቡ ብዙ ብዙ እምነቶች አሉ ተቀብሎ ያምናል፡፡ በሙስሊምም የሚሆነው ይሄ ነው፡፡ ዋህቢያ መጣ፣ ሳላፊ መጣ ሌሎችም ሌሎችም ሺሀ ሊነሳ ይችላል፡፡ ይሄ እንግዲህ መንግስትም ይሁን ማንም ሊያቆመው አይችልም ይሄንን ዝንባሌ፡፡ መንግስት ማድረግ ያለበት እነዚህ አስተያየቶች፣ እነዚህ መስመሮች፣ ከህገ መንግስቱ ወጥተው፣ ሰላም እንዲኖር፣ መረጋጋት እንዳይጠፋ መቆጣጠር እንጂ ከዛ ባለፈ ይሄ እምነት ነው ትክክለኛ ይሄ ደግሞ ትክክለኛ አይደለም ብሎ መናገር መብቱ አይደለም፡፡ ማስተማርም የለበትም፡፡ ግን ኢህአዴግ ትንሹን ነገር አግዝፎ ስለሚያየው ነው፡፡ ኢህአዴግ መንግስት ሆኖ ከግለሰብ ጋር እየተጣላ የሚውል መንግስት ነው፡፡ በጣም ነው የሚያሣዝነው፡፡ አይንቀውም ትንሽ ነገር ነው እቆጣጠረዋለሁ ብሎ አያምንም፡፡ ሰራዊትይዞ ፣ ስፍር ቁጥር የሌለው ፌድራል ፖሊስ ፣ የክልል ፖሊስ፣ የፀጥታ ኃይሎች ይዞ እያለ በሁለት ሦስት ሰዎች እየተሸበረ ነው ያለው፡፡ ኢህአዴግ ሽብር ነው ውስጡ ያለው፡፡ ስለዚህ በሙስሊሙ ይሄ ነገር ሲነሳ ይሸበራል፡፡ ሲሸበር ደግሞ ለዚህ ምላሽ የሚሰጠው በማተራመስ ነው እንጂ ነገሮችን ከስትራጄክ አንፃር አያያቸውም፡፡ ሰልፍ ያስወጣል፣ አገሪቱን በሙሉ በስብሰባ ያስወግዛል፣ በየቀበሌው ፣በየከተማው …. አውግዙ ይሄ መፍትሄ አይሆንም ፣ ሰልፍ ውጡ ይሄ ፕሮፖጋንዳ ነው፡፡ከፕሮፖጋንዳ በዘለለ ነው መታየት ያለበት፡፡ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ሲነሱ በስትራ
ቴጂክ እንጂ በፕሮፖጋንዳ ሊፈቱ አይችሉም፡፡ ምን ማለቴ ነው የአባይ ጉዳይ ሲነሳ ያነሣነው ነገር ነበር፡፡ አባይን ስንነካ አንድ ስትራቴጂክ ጉዳይ ነው ለኛ …. ስትራቴጂክ ጉዳይ ስለሆነ በአንድ ፓርቲ ፣ በአንድ ክፍል ብቻ መፍትሄ የሚያመጣ አይደለም፡፡ መግባባት ያስፈልጋል፡፡ ተቃዋሚዎች ሁሉ ለዚህች ሀገር ኃላፊነት አለብን የሚሉ ተግባብተው መሄድ አለባቸው፡፡ ምክንያቱም ይሄንን ትልቅ ነገር ከነኩ በኋላ ተባብረው መስራት እንጂ የሚያስፈልገው እንዲሁ “አካኪ ዘራፍ” ብሎ ማሰናበት አይቻልም፡፡ የሙስሊም ጥያቄ ሲነሳ እኔ ኢህአዴግ እንደሚያየው አያስደነግጠኝም፡፡ ያን ያህል የሚያስደነግጥ ፣ የሚያስፈራ፣ የሚያሸብር ነገር የለም፡፡ መቆጣጠር የሚቻል ነው፡፡ ያም እሱ በሚያስበው ችግር ቢኖራም፣ እሱ ባወጣው የፕሮፖጋንዳ አቅጣጫ መመራት ሣይሆን ፣ እስቲ እንነጋገርበት ሙስሊሞችን ሲያነጋገር አንዱን ክፍል ብቻ ማነጋገር የለበትም፣ ሁሉንም አነጋግሮ መፍታት ይችላል፡፡ ከተቃዋሚዎችም ጋር ቢሆን መቶ በመቶ የሚቃወሙትንም ማነጋገር እንጂ የራሱን ደጋፊዎች ብቻ አንድ የዩንቨርስቲ ምሁር ማናገር ተገቢ አይደለም፡፡ ስለኔ ምን ይላል ብሎ የተለየ ሀሣብ ሊያገኝ ይችላል፡፡ ስለዚህ የሙስሊሙም ጥያቄ ከአጠቃላይ የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ጋር ተያይዞ መታየት ያለበት ነው የሚመስለኝ

Tuesday, August 27, 2013

ሶስቱ ላሞች እና ኢትዮጲያውያን


በአንድ ወቅት ማንም ጠላት ያልደፈራቸው ጥቁር....ዳልቻ ወይም ቡኒ.....ነጭ.....ላሞች ነበሩ የጥንካሬያቸው እና የመከበራቸው ሚስጥር አንድም ጠቢብ ሆው በሌላም በኩል በብዛታቸው ጠንካራ ሆነው ነበር........ ጥበባቸው ሶስቱ ምግባቸውን በብዛት ለማግኘት እና ጠላት ሲመጣ ያማናቸውንም የዋላ ክፍል እንዳያገኝ ቀጣቸውን ገጥመው ሳር መጋጣቸው እና አንዱ አንዱን የመጠበቅ ዘዲያቸው ነው .....አያ ጅቦ ከጎደኞቹ ጋር ይሆን እና ላሞቹን ሊበላ ይመጣል ላሞቹም በፈጠሩት የመተባበር ጥንካሬ በጠላሉ ጅቦቹን በፊት እግሮቻቸው እረግጠዋቸው አባረሮቸው በሁለተኛውም ቀን እንደዛው ሊበሉአቸው አስበው ሳይሳካላቸው ኤዱ በሶስተኛውም ቀን እንደዛው ሳይሳካላቸው ኤዱ...ከዛ ከየፍጥረቱ ብል አይጠፋም እና አንዱ የጅቦች ብል አንድ አሳብ አለኝ አላቸው እና ለጎደኞቹ ብላቱን እንዲ በማለት ነገራቸው ....እዚ ላሞች እንዳንበላቸው ዘዴ ተጠቅመውብናል ምክንያቱም በመጀመሪያ ሶስት ሆነው የሶስት ላም ጉልበት ማግኘታቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከዋላ ዘርጥጠን እንዳንበላቸው ቂጣቸውን ገጥመው አንዱ የሌላውን በመጠባበቃቸው ነው አለና ለጎደኞቹ ሲነግራቸው እና ምን እናርግ አሉት ጎደኞቹ ከዛ አያ ጅቦ ኮፈስ በማለት መከፋፈል ነዋ አላቸው እንዴት ሲሉት ዘዴ አለኝ አላቸው እና ተከተሉኝ አላቸው ጎደኞቹን ከዛ ወደ ላሞቹ በመቅረብ እንደምን አመሻችው ላሞች ሲላቸው በመገረም ደና እድዚያብኤር ይመስገን ብለው መለሱላቸው ለጅቦቹ ከዛ ጅቡ ጉሮሮውን ጠረግ አድርጎ ዛሬ ልንበላችው አይደለም የመጣነው ነገር ግን አንድ ነገር ልንነግራችው ነው የመጣነው እሱም ለናንተ የሚጠቅም ነው ብለን እናስባለን ከተጠቀማችውበት አለና ፀጥ አለ የነሱን ይሁንታ ለማግኘት ከዛ አንዱ ላም ከማህከላቸው ምንድነው ነገሩ ብሎ አያ ጅቦን ሲጠይቀው አያ ጅቦም እየውላችው ዘመዶቼ እኛ እኮ ወደናንተ ስንመጣ እኮ ነጩአ ላም እየታየችን ነው እሳ ባትኖር እኮ በመአከላችው እኛም እናንተን ለመብላት አንመኛም እናንተም በሰላም ሳራችውነ ትግጣላችው አላቸው እና ደና እደሩ በለዋቸው ኤዱ ከዛ ቡኒው እና ጥቁሩ ላም ይጠራሩ እና አያ ጅቦ ያለው እኮ ትክክል ሳዮን አይቀርም ነጩ ጎላ ብሎ ነው የሚታየው ከኔ እና ካንተ ከለር አሉ ከዛ ለምን አናባረውም አሉና አባረሩት እነ አያጅቦም በቀላሉ ቅርጭም አድርገው በሉት በሁለተኛው ቀንም መጡ እና ሁለቱን ሊበሉ ሲያስቡ አቃታቸው ከዛ ያንኑ ዘዴ ተጠቅሞ ለላሞቹ እኛ እኮ የምንመኛው ቡኒው ከጥቁሩ ስለሚታይ እሱን አይተን ነው የምንመጣው ሲላቸው ጥቁሩ እኔ ለምን በሰላም ሳሬን አልበላም ይል እና ቡኒውን ያባርረዋል ከዛ አያ ጅቦ መጣና ብቻ ለብቻ ቀረጣጥፎ በላቸው የባላል ..............ባውን ጊዜም ቢሆን የትግራዩ ቡድን ወያኔ የአያ ጅቦን ስልት እየተጠቀመ ለ 22 አመት እረግጦ እና ነፃነታችንን ገፎን እየኖረ ይገኛል ...ሆሮሞሁን አማራው የቀድሞውን ስራት ሊመልስብክ ነው........አማራውን ሆሮሞው አገርክን ሊገነጥልብክ ነው.....ጋምቤላውን መሬቱን ሲነጥቀው ለልማት......አፋሩን መሬቱን ለባህድ ሲሰጥበት ሰፈራ......ኦርቶዶክሱን ሙሰሊሙ ሊያርድክ ነው......ሙስሊሙን ኦርቶዶክሱ ስጉሳዊውን ስራት ሊመልስብክ ነው.....እያለ ለ 22 አመት በጥቂቶች የትግራይ ሰዎች እየገዛን ይገኛል ...ነገር ግን ወያኔ በምናባችን ከሳለልን ጠላት ይልቅ እራሱ በጋድ እና በተግባር እዝባችንን በብዙ እጥፍ እየሰቃየው ይገኛል....ስለሆነም ለአገሬ ሰዎች የምላችው ነገር ቢኖር ወያኔ የትግራዩ ቡድን በአሳብ ከሳለልን ጠላትነት ወጥተን አውን በተግባር እዝባችንን ለችግር እና ለነፃነት እጦት የዳረገንን የትግራዩ ቡድን ወያኔ ላይ በአንድነት የምንነሳበት ወቅት ነው በኢትዮጲያ ምድር ማንም የማንም ጠላት አይደለም የሁሉም ቤሮች ገዢዎች ነበሩ የሁሉም ቤሮች ባሮች ነበሩ ወያኔ እድሜውን ለማራዘም ነው ያሎነ ታሪክ ፅፎ ለመግዛት የሚፈልገው ስለሆነም ለአገራችን ነፃነት በሚቀርበን እና የኔን አሳብ በግልፅ ይረዳልኛል በምንለው የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ ታቅፈን ወይም ደግሞ የግላችንን አስተወፆ እያደረግን የትግራዩን ቡድን የሆነውን ወያኔን መታገል ይኖርብናል........እንደ ላሞቹ አንሞኝ ጅቦቹ ብቻ ለብቻ እንዳይበሉን አንድ እንሁን ከነፃነት በዋላ ሁሉም ሰው በነፃነት የፈለገውን ነገር ማከናወንም ሆነ ማድረግ ይችላል....አንድነት አይል ነው...
........በልጉ ካሳ ከኢትዮጲያ አዲስ አበባ.....

ሰበር ዜና “ወልቂጤ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ዋለች”

“ወልቂጤ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ዋለች”
የወልቂጤ ከተማ ፍትሕና ፀጥታ ቢሮ እና የከተማችን ደህንነት ቢሮዎች የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊ የመብት ጥየቃ ጉዞን መግታት አልቻላቹምበሚል እጃቸውን እንዲያወጡ ተደርጎ በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሞች ወቅታዊ ጉዳይ ክትትል ሙሉ በሙሉ ለፌደራል ደህንነቱ አቶ “ከድር ሽኩር” ለተባለው ግለ ሰብ መተውና ከፌደራሉ ዋና መስራያ ቤት በተላኩለት ፌደራል ወታደሮች በመታገዝ የከተማችንን ሙስሊም ወጣቶች እያሰሰ ወደ ወህኔ እየጣለ ይገኛል :
ዛሬን ጨምሮ ያለፉት አራት ቀናት ከተማችን በወታደሮች ስትታመስ ነው ዉላ የምታድረው:
በዚህ አራት ቀን 5 ሙስሊም ወንድሞቻችንለእስር ተዳርገዋል: እነርሱም የት እንደተጣሉ ማንም ሊያቅ ካለመቻሉ ባሻገር እጅግ አሰቃቂ ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል:
አላህ ይርዳን ዱዓ አድርጉልን!!

Thursday, August 22, 2013

ሰበር ዜና በአሜሪካ ግቢ ቦምብ እላያችን ላይ ሳይፈነዳብን ተገኘልን


በአሜሪካ ግቢ ቦምብ እላያችን ላይ ሳይፈነዳብን ተገኘልን

"
ምስጋና ለኢትዬጲያ ፌደራል ፖሊስ እና ለብሄራዊ መረጃ እናደህንነት ኤጀንሲ ጥምር የጸረ ሽብር ቡድን ግብረ ሃይል" 
በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ከተማ በተለምዶ በአሜሪካግቢ ራስ ስዩም ሆቴል አጠገብ ወደ አርባምንጭ ከተማ ጭነትየሚጫንበት ቦታ አካባቢ በሚገኘው ራህመት ኤጀንሲ በር ላይ ኮድየታርጋ ቁጥር 73189 በሆነ አንድ |የጭነት ማመላለሻ አይሱዙጎማ
ስር የአጅ ቦምብ ተገኘ ተባለላቹ፡፡፤ ይህን የእጅ ቦምብ የአዲስአበባ ከተማ መደበኛ ፖሊሶች ቀደም ብለው በእጃቸው ይዘውትእንደነበር የአይን እማኞች ገልጸዋል፡፤የእጅ ቦምቡን ጠዋት ይዘውት ከነበሩት ሁለት ፖሊሶች መካከል የአንዱ ፎቶ ከዚህበታች ተያይዞ ቀርቧል|፡፡ሙስሊሙ የመረጃ ሰው ሆኗል፡፡አልሃምዱሊላህ ይህ ቦምብ አፈንጂው እና ቦምባ አምካኞችያደረጉት ትንቅንቅ አንድ ወንድም ያደረሰኝን መረጃ ላካፍላችሁ፡፡ የተቀረውን መረጃ በቦታው ከነበሩ እና ከኢቲቪ ማጣራትትችላላችሁ

"
አንድ ግለሰብ ቦምብ ይዞ በመምጣት አንድ የጭነት መኪና ጎማ ስር ቦምቡን አስቀምጦ ዞር ይላል፡፤ በመቀጠልም ይህግለሰብ ከቆይታዎች ቡሃላ ተመልሶ በመምጣት እዛው አካባቢ ይቆማል፡፡ በመቀጠልም ፖሊስ ይህን ግለሰብ በቁጥጥር ስርያውለዋል፡፡ከዛ ፖሊስ ይህን ግለሰብ ሲፈትሸው ሌላም ቦምቦች በኪሱ ስር ያገኛሉ፡፡ ከዛ የፌደራል ፖሊስ እና የብሄራዊመረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ የጸረ ሽብር ግብረሃይል ይህን አሸባሪ ግለሰብ በህዝብ እና በንብረት ላይ ጉዳት ሳያደርስበቁጥጥር ስር አዋሉት፡፤
ከዛ የፈንጂ አምካኝ ግብረሃይል መጣና መኪናው ጎማ ስር የተቀመጠውን ቦምብ እንዳይፈነዳ በጥንቃቄ በማድረግ አክሸፈው፡፤ከዛ በቃ ድራማው በሚገርም ሁኔታ በመጠናቀቁ ቀረጻ ተካሂዶለታል፡፡ በጥሞና ስላነበባችሁልኝ አመሰግናለው"
ቆይ ትንሽ ልጨምርላችሁ ይህ አሸባሪ ግለሰብ እራሱ ያስቀመጠው ቦምብ ጋር በመምጣት መፍንዳት እና አለመፈንዳቱንየሚጠባበቀው ምንኛ አስገራሚ አሻባሪ ነው???? ቀጥሎም ለሌላ ተልኮ የሚሆን ቦምቦችን በኪሶ ሸክፎ ይዞ ነበር፡፤ይህንንምአደገኛ ሊፈጸም የነበረውን የሽብር ጥቃት በማስመለከት ለኢቲቪ ዜና የሚሆን ድራማ ይህ አሸባሪ ግለሰብ ከፌደራል ፖሊስእና ከብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ የጸረ ሽብር ግብረ ሃይሉ ጋር በመሆን ሲከውን እንደነበር የአይን እማኞችገልጸዋል፡፡ የዚህን ሙሉ ዜና ዝርዝር ማታ ኢቲቪ ዜና ላይ ይጠብቁ:;
ከዚህ ቀደም በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያም ተመሳሳይ ጠቀጣጣይ የሆኑ ሁለት ስሊንደሮች ተቀምጠው መገኘታቸው ኢቲቪዘግቦልን ነበር፡፡ደሞ ሌላ ቀን ምን አይነት ነገር መያዡን እንሰማ ይሆን???? ፡፡
ምናለ ኢትዬጲያ ሃገሬ ለአለም ሰላም ሁሌም በምታደርገው ጥረት የምትደነቅ በመሆኗ እንዲህ አይነት የፀረ ሽብር ግብረሃይሏን ችሎታ ለሌሎች ሃገሮችም ልምዷን ብታካፍል እና ቦምቦች ሳይፈነዱባቸው ሁሌም ከነአሸባሪው በቁጥጥር ስር እንዲያውሉ ብትረዳቸው ?????
እኔስ ምንም አልልም ግን ብቻ ይሄ ድራማ እንዲ እያጃጃለን አንድ ቀን የምር አፈንድተውት እንዳይጨርሱን እሰጋለው!!!
ለማንኛውም ቦንቦቹ ሳይፈነዱ በቁጥጥር ስር ስለዋሉ አልሃምዱሊላህ በዚህኛው ድራማ ሂወታችንን አልቀጠፉብንም፡፡
አላህ የኢትዬጲያን ህዝብ ለድራማ ተብሎ ከሚደረስ ጥቃት ይጠብቅልን!!!!