Sunday, October 27, 2013

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ ኤርትራ በተገነጠለችበት ወቅት መሆን ያለበት ይህ ነበር።

ትክክለኛው የኢትዮጵያ ካርታ፡ በሊግ ኦፍ ኔሽን የሚታወቀውና፡ እንደአውሮፓ አቆጣጠር በ1961 የተባበሩት መንግሥታት ካጸደቃቸው ሦሥቱ የኤርትራ ሁኔታ ውሳኔ፡ ” ኤርትራ የፊዴሬሽኑን ሁኔታ ሕዝቡ ካልፈለገና ካርታዋ ከተገነጠለች፡ ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽን ወደሚታወቀው እዚህ ላይ ወደሚታየው ካርታዋ ይመለሳል ነበር። 
የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሽስት ወያኔ ሞተር መለስ ዘባንዳዊ፡ ወደብ ሸቀጥ ነው በሚል የብልግናና የውንብድና ንግግሩ፡ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉትን የግብር ገንዘብ ለጂቡቲ በቀን ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገብር ታውቃላችሁን? 
በውጭ ሃገር የሚገኘው ታላቁ የኢንተርኔት ሚዲያ ” ኢትዮሚዲያ ” በፊተኛው ገጹ ላይ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” በማለት ለተወናበደው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ ነው።በትክክለኛው በነአጼ ምኒልክም ይሁን በሊግ ኦፍ ኔሽን እንዲሁም የኤርትራ ፌዴሬሽን በጸደቀ ወቅት መገንጠልን ሕዝቡ የሚፈልግ ከሆነ፡ በተባበሩት መንግሥታት የሚታወቀው ይኸው ካርታ ነው። ወያኔዎች ስለድንበርም ይሁን ስለባሕር በር የመሃይማን፤ የጫካ አፈራሽ ዱርዬዎች ናቸው።
መለስ ዘባንዳዊ ወደብ ሸቀጥ ነው ብሎ ለጂቡቲ በቀን 6 ሚሊዮን ብር የኢትዮጵያ ሕዝብ የግብር ገንዘብ እንዲጠፋ ያደረገውና ኢትዮጵያን ጭለማ ያደረገው።
ታላቁ የኢትዮጵይውያን የውጭ ኢንተርኔት “፡ኢትዮሚዲያ የፊት ገጽ ላይ የተጻፈው፦ ” ከአርባ ግድብ አንድ ወደብ ” እውነት ነው። በወያኔ ኢትቪና ሌላችም ፕሮፓጋናዳዎች የተወናበደው በተለይም የመከላከያ ሠራዊት ነኝ ለኢትዮጵያ ቆሜያለሁ የሚል ካለ እውነታው ይኸው ነው።
Fresenay Kebede

Residents in Gambella set Indian-owned farm on fire

420013_215543375240044_2099309808_n
oct27,2013
Residents of the Gambella Regional State, Godera woreda, attacked and set the property of the Indian farm, Verdanta Harvest Plc., on fire on account of destroying the rich forest resources in the woreda where Verdanta has some 5,000 hectares for tea plantation.
According to sources in the area, the vigilantes attacked the plantation compound on Tuesday late night and set ablaze stores, fuel tankers, machineries like tractors and excavators and logs of timber, allegedly harvested from the land the company took for tea plantation. Gatlowak Tute, president of the region, confirmed the occurrence and said that a 9-man team has been sent to the area to investigate the event. “So far, security forces have taken into custody few locals suspected of involvement in the incident,” Gatlowak told The Reporter.
Verdanta took over the plantation five years ago from the Ministry of Agriculture on a 50-year lease contract with fairly cheap terms. According to the contract signed at the time, the company agreed to pay 111 birr annual lease price for the plantation extending 3012 hectares wide in Godera woreda and Gumare kebele. The total lease quotation of 16.7 million birr was agreed to be payed over the course of the 50 years at 334,332 birr per annum.
However, Verdanta requested the land for tea plantation before the ministry took over the land provision from the region and hence was able to receive 5,000 hectares although the contract with ministry say 3012. According to sources, the company have kept control of the 5,000 hectares until present, which residents of the area consider to be a forest resource and national forest region. The two kebeles of Godera woreda, Gomare and Kubu, are among the 58 primary national forest regions in the country. According to residents in the locality, the area is also rich in forest agricultural productions like honey, spice and coffee.
The vigilant residents say that the plantation company was offered is indeed a forest area that deserves to be preserved. Whereas both the regional government and the ministry say that the plot of land is no more than scattered bushes and that it does not qualify to be called a forest. According to the Food and Agricultural Organization (FAO) standards, a forest area can be referred to as such as long as it is at least half a hectare wide and have trees more than five meters tall. Residents say that even the plot that is held by the Verdanta is 5,000 hectares and that it has tree which are 10 meters tall in length. At one time former president of the republic, Girma Woldegiorgis appealed to both the ministry and the region not give the land which should be preserved as national forest area. Tea plantation require the entire vegetation to be cleared out from the area, hence the president appealed to reconsider the decision. However, both the ministry and regional administration did not want to accept the request and hence the company stayed in possession of the property until the incident.
On the other had, the widespread rumors accusing the Verdanta of harvesting timber from the forest while it was supposed to be planting tea was also not accepted by the authorities. Sources say that on quite various occasions authorities have discovered logs of timber products leaving the property of Verdanta. However, the regional president did not deny this but said that the company have has assured his administration that the timber is not for sale. Although not verified by the findings of the investigating committee yet, sources indicate that it was the vigilantes of Godera who have taken matters into their own hands.
Development Bank of Ethiopia (DBE) have provided 89.5 million birr in loans to Verdanta. Hence, some are asking if DBE collateral has been damaged in the process. Efforts to get response from the Bank was not fruitful, and other are also asking if the investigative committee could come up with an amicable solution for the residents and the company in question.

የትርፍ ሰዓት ትግል


ኢዮብ ይስኃቅ
ከዕለታት አንድ ቀን ባልተለመደ ድፍረት የሙስና ኮሚሽን ሰይፉን ትላልቅ የወያኔ ባለሥልጣናት ላይ አሳረፈ። እንደመድኃኒት ብልቃጥ እዚህም እዚያም ተወሽቆ የነበረ ብርና ንብረት እያስቆጠረ ወንጀለኞቹን ዋስ እየከለከለ ወደ ወህኒ ወረወረ። ሚኒስትሮች ከቦታቸው ተፈናቀሉ፤ የሙስና እናት የሚለውን ሜዳሊያ ያጠለቀችው ወ/ሮ አዜብ ከኤፈርት ተባረረች። ያዲሳባ ከንቲባነትም ሱሚ ነው ተባለች። ከሁለት ብቻ ሳይሆን ከብዙ ያጣች ሆነች። ህዝቡ እልል ለማለት ቢፈልግም ወያኔን ስላላመነ መጨረሻውን ለማየት መጠባበቅ ያዘ።
 የተፈራው አልቀረም ጉዱ ቀስ በቀስ ይወጣ ጀመር። በትሩ አንደኛው ጠንካራ ሙሰኛ ሌላኛውን ደካማ ሙሰኛ የሚያስገብርበት ሂደት ነበር። ህወሓትን ሊጋፋ ይችላል ተብሎ የተጠበቀው በረከት ስምኦን ጉዋደኞቹን ካስበላ በኋላ ተደራድሮ ለሌላ ሥልጣን ታጨ። ምናልባት ትግርኛ መናገሩ ከአደገኛው ሰይፍ ሳይታደገው አልቀረም – ለዛሬ።
ሰሞኑን የተስፋዬ ገብረአብ እና የተመስገን ደሳለኝ ከቅርብ ምንጮች ተገኘ ተብሎ የተጻፈውን የኢህአዴግን መበላላት የሚያሳይ ጽሑፍ ሳነብ፤ በተጨማሪ የተገነዘብኩት ነገር እስሩና መጠላለፉ ለሀገሪቱ ጥቅም ሳይሆን የወያኔን የሥልጣን ግዜ ማራዘሚያ መሆኑን ነበር። በተለይ ተመስገን አቶ ስብሃት ነጋ “በውራይና” ጋዜጣ ላይ የፃፉትን ሲያስነብበን የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር በፍፁም ሥልጣኑን የማስረከብና ለኢትዮጵያም ምንም አይነት የሚጠቅም ራዕይ እንደሌለው ያረጋገጠ ነበር። ምናልባት ራዕይ እንኳን ቢኖራቸው፤ በሥልጣን ላይ እስከነድዳቸው የመቆየት ሊሆን ይችላል። መቆየታቸው ባልከፋ! ነገር ግን ለዚች ድሃ ሀገርና ህዝብ የሚጠቅም አንድም ፖሊሲ የመቅረፅ ሃሳብ የላቸውም። እያንዳንዱ ልማት ተብዬ ከጀርባ ለነሱ ሙስና የተጋለጠ ካልሆነ በስተቀር ለሀገር ተብሎ የሚወጣ ዕቅድ የለም። ለሰው ልጅ ምን ያህል ሀብት ይበቃዋል ብለን እስክንገረም ድረስ በአጥንቱ የቀረውን ህዝብ እየጋጡት ይገኛሉ።
የመገናኛ ብዙኀኖቻችን
ባለፉት ሃያ ዓመታት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ስንመለከት በአዲስ ዘመንና አጋር የመንግሥት ሚዲያዎች እንደሚነገረን የጥጋብ ሀገር አልሆነችም። ወይንም በዘመናዊው አዲስ ዘመን “ሪፖርተር” ጋዜጣም እንደሚቀርብልን የኢትዮጵያ ችግር የጠንካራ ተቃዋሚ መጥፋት ብቻ አይደለም። ስታትስቲክ ብቻውን ዜና አይደለም ብሎ በአሉ ግርማ እንዳለን፤ የተመደበውን በጀት ድምር፣ የሚሠሩ ልማቶች ወጪና የተገኘውን ብድር በደማቅ ርዕሶች መፃፍ ብቻውን ጥሩ ጋዜጣ አያሰኝም። በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ድህነት፣ በየትምህርት ቤቱ ለሁለትና ለሦስት ቀናት እህል ባፋቸው ሳያልፍ በየክፍላቸው የሚወድቁትን ህፃናትና በየቀኑ በልማት ስም የሚፈናቀሉትን ቤተሰቦች ዜና እንደግል ጋዜጣነቱ ሲያስነብበን አናይም። አልፎ አልፎ ተኝቶ ቤቱ ድረስ የሚቀርቡለትን ትኩስ መረጃዎች ለማጀብ ቀላል ትችቶችን በርዕሰ አንቀፁ ያቀርብልናል።
እንደአለመታደል ሆኖ በሌሎችም የግል ጋዜጦች የምናገኘው ዜና ጽንፈኝነትን የተሸከመ ከመሆኑም ሌላ መንግሥትን ከመሳደብ ውጪ በተቃዋሚ ጎራ ያለውን ችግር ግልፅልፅ አድርገው አያቀርቡም። እየተሳደደም ቢሆን ሁሉንም በአንድ ሚዛን የሚያስቀምጠው አንድ ለናቱ የሆነው ተመስገን ደሳለኝ ብቻ ነው።
በሀገር ውስጥ ያለው ተቃዋሚ
በርግጥም ወደ ተቃዋሚ ጎራ ስንመጣ ቀላል የማይባል ችግር አለ። በመጀመሪያ ባገር ውስጥ ያሉትን ስንመለከት አብይ ችግር ሆኖ የምናገኘው ሥልጣንን ሙጭጭ የማለት ጉዳይ ነው። የሊቀመንበርነቱን ቦታ አስረከቡ ሲባል አረፍ ብለው ይመለሱበታል። በዚህ ሃያ ዓመት ውስጥ የትኛውም አንጋፋ ፓርቲ በአዲስ ወጣት መሪ ተተክቶ አላየንም። ተተካካን ያሉትም በአጋፋሪነት ከኋላ በምክትልነት ያስከተሉዋቸውን ሰዎች ነው። እነዚህ ሰዎች እንደአስፈላጊነቱ ቦታውን ሊለቁ የሚችሉ ታማኝ ሰዎች ናቸው። በተቃዋሚነት ዘመኑ ዲሞክራሲን ያላለማመደን መሪ በአጋጣሚ የመንግሥት ሥልጣን ቢረከብ እንዴት አይነት አምባገነን እንደሚሆን ለመገመት ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም። ለጠንቋዩ የታሰበውን እራሳችን እየበላን እራሳችን እንገምታለን።
 ስደተኛው ተቃዋሚ
ወደውጪው ተቃዋሚ ስንመጣ ሰሞኑን “ሰላቢ ፀሐፊዎች” በሚል በተስፋዬ ገብረአብ የቀረበውን ጽሑፍ በማስታወስ ነው። ተስፋዬ ይህን ያለው በብዕር ስም ጎርፍ የሚለቁትን ፀሐፊዎች ለመንካት ነው። እኛ ደግሞ ሰላቢ ፖለቲከኞች እንላለን – ቁርጠኝነት ጎሎዋቸው የሌላውን የትግል ስሜት ይሰልባሉና። በትክክል የምንስማማበት አንድ ነጥብ አለ። ይኸውም ኢትዮጵያ ፋታ በማይሰጥ አጣብቂኝ ውስጥ እንዳለች። ይህ ማለት ማቄን ጨርቄን ሳንል የምናምንበትን ወይም የምንሰብከውን ትግል መከተል ይሆናል። ወድድንም ጠላንም የዛሬዎቹ መሪዎች በረሃ በገቡበት ወቅት ወጣትነታቸውን ጨምሮ ብዙ ጥቅሞቻቸውን መስዋዕት አድርገው ነው።
ለምሳሌ መለስን እና ኢሳያስ አፈወርቂን ብንወስድ፤ አንዳቸው የተከበረ ዶክተር፣ ሌላኛቸው ደግሞ ኢንጅነር የመሆን ተስፋ የነበራቸው ወጣቶች ነበሩ። በሀብትም ቢሆን ደጃዝማች አባቶቻቸው መሶባቸው ሙሉ፣ ጎተራቸው ካመት ዓመት የማይጎድል ባላባቶች ነበሩ። ጥሩ ኑሯቸውንና የነገ ትልቅ ሰው የመሆን ዕድላቸውን በሳጥን ቆልፈውበት ነው ወደ በረሃ የገቡት። አይ! አሸንፈው መሪ ለመሆን ነው የሚል የዋህ ያለ አይመስለኝም። ኃይለሥላሴም ሆኑ ደርግ ይወድቃሉ ብሎ እንኳን ሰዉ እግዜሩም እርግጠኛ የነበረ አይመስለኝም። የራሱን ጀግኖች እየበላ መንገዱን ጠርጎ ያስገባቸው ወደድንም ጠላንም ኮሌኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ነው።
ይህ እንዲህ ሆኖ ሳለ የዛሬዎቹ ተቃዋሚዎች በተለይ ደግሞ ብቸኛው አማራጭ የትጥቅ ትግል ነው የሚሉት፣ እንኳን ሕይወታቸውን፣ ደሞዛቸውን ሲሰዉ አናይም። ኢትዮጵያ ያለችበት ችግር አጣዳፊና ግዜ እንደማይሰጥ ከተስማማን ፈጣን እርምጃ መወሰድ ነበረበት። ከዚህ ይልቅ መግለጫዎችን በመስጠቱ ላይና ገቢ ማሰባሰቡ ላይ በርትተው ሲንቀሳቀሱ እያየን ነው።
ከጥቂት ዓመታት በፊት በድል ማግስት አዲስ አበባ የሚያስገባ ካርድ በገንዘብ የሚታደልበት ዝግጅት ተደርጎ ነበር – በግንቦት ሰባት። በዚህ አጭር ጊዜ ወያኔ ወድቆ አዲስ አበባ ይያዛል የሚል የየዋህ ግምት ባይኖረኝም በኢትዮጵያ ተራሮችና ጫካዎች ውስጥ እየተሽሎከለከ ወያኔን የሚያሸብር ታጋይ መጠበቄ አልቀረም። በኢንተርኔት መስኮቶች ወዛቸው ግጥም ያለ ባለስካርፍ ታጋዮችን ተመልክተናል። ግን የዋሉበትን የትግል አውድማ በስህተት እንኳን ሰምተን ወይንም አይተን አናውቅም።
አንድ እየተሠራ ያለ ነገር ቢኖር ይሔ እንደጉድ ድህነትንና ግፍን እየሸሸ በረሃና ባህር የሚበላው ወጣትና ወደ ዐረብ ሀገር የሚሰደዱ እህቶች ምርጫቸው ሽሽት ሳይሆን የችግሮቻቸው ምንጭ የሆነውን መንግሥት ለመጣል ትግሉን መቀላቀል ነበር። ይህ መሆኑ ቀርቶ ግን በኢትዮጵያ ጫካዎች ልናያቸው የሚገቡ ወታደራዊ ልብሶች እንደእንቁጣጣሽ ቀሚስ እነታማኝ በየነን በፈንድሻ ለመቀበል በየስደቱ መድረክ ላይ ሲጌጥባቸው እናያለን።
 ኢትዮጵያን ከህወሓት ጥፋት ለማዳን ያለን ምርጫ
ሀገራችን በህወሓት መራሹ መንግሥት እጅ ከቆየች ያለማጋነን በሚቀጥሉት ዓመታት ዛሬ ያለችበት ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እንደማይኖራት ማወቅ አለብን። ህዝቡም በዘርና በኃይማኖት ተከፋፍሎ እርስ በእርሱ የሚበላላባት ምድር ትሆናለች። ስለዚህም የትርፍ ጊዜ (part time) ትግል ለዚች ሀገር እንደማይመጥን አውቀን የመረጥነውን የትግል መስመር በቁርጠኝነት መቀጠል አለብን። በሰላማዊ ከሆነ በሰላማዊ፣ በትጥቅ ትግል ከሆነ በቦታው እታች ወርዶ መታገል ያስፈልጋል። ይህ ካለሆነ ግን የቁርጠኛ ልጆችን መንገድ በመሪነት ስም በመዝጋት በእጅ አዙር የወያኔ መንግሥት ዕድሜ እንዲራዘም ማገዝ አይገባም።

ትንሽ መልዕክት ለተስፍሽ (ተስፋዬ) ገብረአብ
በመጨረሻ ከላይ ስሙን ለጠቀስኩት ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ የምለው አንድ ወንድማዊ ምክር አለ። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ አሁን በቅርብ ደግሞ ለላይፍ መጽሔት በሰጠው ቃለመጠይቅ ስለኤርትራ ለምን እንደማይፅፍ ተጠይቆ “ሰዎች የማላውቀውን እንድጽፍ ለምን ይጠብቃሉ” የሚል መልስ ሰጥቷል። ወይንም በሚቀጥለው መጽሐፉ በአንዲት ምዕራፍ እንደሚያወጋን ተናግሯል። እኔ ግን የቡርቃ ዝምታን የሚያክል መጽሐፍ ለመጻፍ አርባጉጉ ወይ በደኖ ካሳለፈው ጊዜ የበለጠ በኤርትራ ቆይቶዋል የሚል ግምት አለኝ። በእናቱ ኤርትራዊ ቤተሰብ ውስጥ ማደጉ የኤርትራዊያንን ሕይወትና ኑሮ ከሌላው ሰው በተሻለ የማወቅ ዕድሉ አለው። ለአንድ አይደለም ለዕድሜ ልኩ የሚበቃ መጽሐፍ የሚወጣው ግፍ በኤርትራ ምድር እየተፈጸመ ነው። ተስፍሽ ደራሲ ድንበር እንደማይወስነው ላንተ መንገር የለብኝ። ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለህ ማመንህም ቢሆን ስለጎረቤት ሀገር ህዝብ መበደል ስለመጻፍ ሊገታህ አይገባም። ብዕርህ ስለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ስለመላው አፍሪካ ህዝብ መዘመር ይገባታል።
ይህቺን ትንሽ ጽሑፍ ከጫርኩ በኋላ በኢንተርኔት የተለቀቀውን “የስደተኛው ማስታወሻ” አነበብኩ። ሌላ ጊዜ በሰፊው ብመለስበትም አሁን ተስፋዬን አንድ ቀላል ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ። አሁን ማን ይሙት ከአስመራ ተነስተህ እስከ ናቅፋ ተራራ በደራሲ ዓይን የታዘብከው አስፋልት የሚያቁዋርጡ የደረቁ ወንዞችን ብቻ ነው? አለምክንያት በየድንጋዩ ስር ውሃ እንዳጣ ዛፍ የጠወለጉ ወጣቶችን አላየህም? ወይንስ ያንተን መምጣት አስመለክቶ እንዳታያቸው ደብቀዋቸው ነው? ብዕርህ ደፋርና ግልፅ ናት ብዬ አስብ ነበር፤ ግን የዘር ልጉዋም ሳያደናቅፋት አልቀርም።
እኔ ጨርሼአለሁ።
ነፃነትና ሰላም ለመላው አፍሪካ ህዝብ!

ኢዮብ ይስኃቅ
eyobisack@yahoo.it  

ወ/ሮ አዜብ መስፍን Azeb Mesfin

Monday, October 14, 2013

ወያኔ አንዳንድ የአማራ ክልል ከተሞችን ለራሱና ለሌሎች ለአጎራባች ክልሎች ሊሸልም መሆኑ ተሰማ

ከዚህ ቀደም ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ገንጥሎ ትግራይ ዉስጥ የጨመረዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ያኔ የዘረፈዉ መሬት አልበቃ ብሎት አሁንም በአማራ ክልል የሚገኙ አንዳንድ የድንበር ከተሞችን ወደራሱ ወይም (ትግራይ ክልል) ለመጨመር ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ኢሰት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። የኢሳት ዘገባ በግልጽ እንዳስቀመጠዉ በድንበር አካባቢ የሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች የሚሰጡት ለኢያንዳንዱ አጎራባች ክልል ቢሆንም ወያኔ ይህንን የአማራን ክልል ከተሞች ለአጎራባች ክልሎች ሁሉ የማሸጋሸግ ዕቅድ ያወጣዉ ለይስሙላ እንደሆነና ዋና አላማዉ አማራዉን ለማዳከምና የራሱን ክልል ለማስፋት ነዉ የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። በድንበር አካባቢ ከሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች አስተዳዳሪዎች በተገኘው መረጃ መሰረት የጃን አሞራ፣ የማይጸብሪ ፣ የራስዳሸንና የአዲአርቃይ አካባቢዎች ትግራይ ክልል ዉስጥ የሚጠቃሉ ሲሆን በመተማ በኩል ደግሞ የተወሰነውን ክፍል ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመስጠት ድርድር በመካሄድ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የየከተማዎቹ ባለስልጣናት ለኢሳት በሰጡት መረጃ መስረት ባለስልጣናቱ የህዝቡን የልብ ትርታ አዳምጠዉ የህዝብን ሀዘንና ድንጋጤ የተመለከቱ ሲሆን፣ አንዳንድ የወረዳ ባላስልጣናት ደግሞ የችግሩን ስፋት ኢሳት ለህዝብ ይፋ እንዲያሳዉቅላቸዉ ተማጽነዋል። የወያኔ አገዛዝ ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ስር የነበረውን የመተከል ዞን ለቢኒሻንጉል ጉምዝ ፤ራያና ቆቦን ፤ዳንሻንና ሁመራን በመተማ በኩል ለሱዳን ፤ቀሪውን የመተማ ክፍል ደግሞ ለቤንሻንጉል መሰጠቱን በማውሳት ፣ አሁንም ተጨማሪ መሬት እየተቆረሰ ክልሎችን ለማስደሰት ሲባል ብቻ እኛን እየተጎዳን ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የአንቀጽ 39 ትሩፋቶች የሰጡን ገፀ በረከቶች ናቸው ሲሉ ያማረሩት የድንበር ከተማ ነዋሪዎች ደግሞ ”ጨለምተኛ አባት መሬት እየሸጠ ልጆቹን ርስት ያሳጣል፡፡ ጨለምተኛ መንግስት ደግሞ አገርን በመሸጥ ዜጎችን ያስደፍራል፡፤ ማንነታቸውን ያሳጣል፤ መንግስትም ማንነታችንን እየነጠቀን ነው ሲሉ” በወያኔ አገዛዝ ላይ ያላቸዉን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁኔታው ያበሳጫቸው ነዋሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ድርጅቶች ጉዳዩን አጽንኦት ሰጥተው ሊያዩት ይገባል ብለዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ የትግርኛን ቋንቋ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንዲማሩት ለማድረግ ታስቦ በጎንደር በተካሄደው ፓይለት ጥናት ህዝባዊ ተቃውሞ በማስነሳቱ እንዲቆም ተደርጓል። ይህንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ጥናት ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ባየ ይማም በቅርቡ በአቀረቡት ጥናት የመንግስት ቋንቋ አጠቃቀም ‘የህዝብን ጉዳይ በህዝብ ቋንቋ’ የሚለውን መርህ የተከተለ ባለመሆኑ ህዝቡ ማግኘት ያለበትን መልእክት በትክክል እያገኘ፤ ለለውጥም እየተነሳሳ አይደለም ብለዋል፡፡ ባጭር ቃል በዚህ አይነት ቋንቋ የሕዝብን አእምሮ መቀየር እንደማይቻል የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ባለስልጣናቱ የአማረኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የበኩላቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል፡፡“ሀገራችን የቋንቋ ፖሊሲና የአጠቃቀም ደንብ ወይም ስርዓት እስካሁን የላትም፡፤ እስካሁን ድረስ ከህገመንግስታዊ የመብት ማረጋገጫ አንቀጾች ያለፈ፣ ቋንቋን እንደ ማንኛውም የሀገር ሀብት በእቅድ የሚያሳድግ፣ የሚቆጣጠር፣ አጠቃቀሙን ስርዓት የሚያሲይዝ ፖሊሲና ዝርዝር ደንብ የለንም፡፡ ባለመኖሩም ሁሉም እንደፈለገ የሚተረጉምበት፣ የሚጽፍበት፣ የሚያሰራጭበት ሁኔታ ውስጥ ገብተናል፡፡ ይህ ሊቆምና ቋንቋዎቻችን በዕቅድ ሊያድጉና ጥቅም ላይ ሊውሉ ይገባል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
የአማርኛ ቋንቋ የሀገሪቱ የስራ ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ክልሎች በፍፁም ጥላቻ እንዲመለከቱትና እንዲሁም ክፍል ውስጥ ገብተው የመማርን መብት ለተወላጆች ብቻ ትቻለሁ በማለት የአማርኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ፤ በትግራይ ፤ በኦሮምያና ደቡብ ክልሎች ክፍት እንደሚሆኑ ታዉቋል። ተማሪዎች በቋንቋ ትምህርት በሚመዱበበት ወቅትም በአማርኛ ቋንቋ የሚሰጡ ደጋፊ ትምህርቶችን ላለመማር አሰጣ አገባ እንደሚገቡ ታውቋል፡፡በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በቤንሻንጉል እና ሶማሌ ክልሎች የክልሎቹን ቋንቋ የማይናገሩ ተማሪዎች ተመርቀው ስራ ለማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ከአማራ ክልል የሚመጡ ተማሪዎች ከክልላቸው፣ ከአዲስ አበባ እና ከደቡብ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች ተቀጥረው ለመስራት እየተቸገሩ ነው።አንዳንድ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት ካልሆነ በስተቀር የአማራ ክልል ተማሪዎች ስራ ለመያዝ እንደሚቸገሩ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል። በሌላ በኩል ግን አማርኛ የሚችል የማንኛውም ክልል ተወላጅ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ስራ የመያዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ወያኔ አንዳንድ የአማራ ክልል ከተሞችን ለራሱና ለሌሎች ለአጎራባች ክልሎች ሊሸልም መሆኑ ተሰማ

ከዚህ ቀደም ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ገንጥሎ ትግራይ ዉስጥ የጨመረዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ያኔ የዘረፈዉ መሬት አልበቃ ብሎት አሁንም በአማራ ክልል የሚገኙ አንዳንድ የድንበር ከተሞችን ወደራሱ ወይም (ትግራይ ክልል) ለመጨመር ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ኢሰት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገበ። የኢሳት ዘገባ በግልጽ እንዳስቀመጠዉ በድንበር አካባቢ የሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች የሚሰጡት ለኢያንዳንዱ አጎራባች ክልል ቢሆንም ወያኔ ይህንን የአማራን ክልል ከተሞች ለአጎራባች ክልሎች ሁሉ የማሸጋሸግ ዕቅድ ያወጣዉ ለይስሙላ እንደሆነና ዋና አላማዉ አማራዉን ለማዳከምና የራሱን ክልል ለማስፋት ነዉ የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። በድንበር አካባቢ ከሚገኙ የአማራ ክልል ከተሞች አስተዳዳሪዎች በተገኘው መረጃ መሰረት የጃን አሞራ፣ የማይጸብሪ ፣ የራስዳሸንና የአዲአርቃይ አካባቢዎች ትግራይ ክልል ዉስጥ የሚጠቃሉ ሲሆን በመተማ በኩል ደግሞ የተወሰነውን ክፍል ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመስጠት ድርድር በመካሄድ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የየከተማዎቹ ባለስልጣናት ለኢሳት በሰጡት መረጃ መስረት ባለስልጣናቱ የህዝቡን የልብ ትርታ አዳምጠዉ የህዝብን ሀዘንና ድንጋጤ የተመለከቱ ሲሆን፣ አንዳንድ የወረዳ ባላስልጣናት ደግሞ የችግሩን ስፋት ኢሳት ለህዝብ ይፋ እንዲያሳዉቅላቸዉ ተማጽነዋል። የወያኔ አገዛዝ ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ስር የነበረውን የመተከል ዞን ለቢኒሻንጉል ጉምዝ ፤ራያና ቆቦን ፤ዳንሻንና ሁመራን በመተማ በኩል ለሱዳን ፤ቀሪውን የመተማ ክፍል ደግሞ ለቤንሻንጉል መሰጠቱን በማውሳት ፣ አሁንም ተጨማሪ መሬት እየተቆረሰ ክልሎችን ለማስደሰት ሲባል ብቻ እኛን እየተጎዳን ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የአንቀጽ 39 ትሩፋቶች የሰጡን ገፀ በረከቶች ናቸው ሲሉ ያማረሩት የድንበር ከተማ ነዋሪዎች ደግሞ ”ጨለምተኛ አባት መሬት እየሸጠ ልጆቹን ርስት ያሳጣል፡፡ ጨለምተኛ መንግስት ደግሞ አገርን በመሸጥ ዜጎችን ያስደፍራል፡፤ ማንነታቸውን ያሳጣል፤ መንግስትም ማንነታችንን እየነጠቀን ነው ሲሉ” በወያኔ አገዛዝ ላይ ያላቸዉን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁኔታው ያበሳጫቸው ነዋሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ድርጅቶች ጉዳዩን አጽንኦት ሰጥተው ሊያዩት ይገባል ብለዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ የትግርኛን ቋንቋ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንዲማሩት ለማድረግ ታስቦ በጎንደር በተካሄደው ፓይለት ጥናት ህዝባዊ ተቃውሞ በማስነሳቱ እንዲቆም ተደርጓል። ይህንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ጥናት ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ባየ ይማም በቅርቡ በአቀረቡት ጥናት የመንግስት ቋንቋ አጠቃቀም ‘የህዝብን ጉዳይ በህዝብ ቋንቋ’ የሚለውን መርህ የተከተለ ባለመሆኑ ህዝቡ ማግኘት ያለበትን መልእክት በትክክል እያገኘ፤ ለለውጥም እየተነሳሳ አይደለም ብለዋል፡፡ ባጭር ቃል በዚህ አይነት ቋንቋ የሕዝብን አእምሮ መቀየር እንደማይቻል የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ባለስልጣናቱ የአማረኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የበኩላቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል፡፡“ሀገራችን የቋንቋ ፖሊሲና የአጠቃቀም ደንብ ወይም ስርዓት እስካሁን የላትም፡፤ እስካሁን ድረስ ከህገመንግስታዊ የመብት ማረጋገጫ አንቀጾች ያለፈ፣ ቋንቋን እንደ ማንኛውም የሀገር ሀብት በእቅድ የሚያሳድግ፣ የሚቆጣጠር፣ አጠቃቀሙን ስርዓት የሚያሲይዝ ፖሊሲና ዝርዝር ደንብ የለንም፡፡ ባለመኖሩም ሁሉም እንደፈለገ የሚተረጉምበት፣ የሚጽፍበት፣ የሚያሰራጭበት ሁኔታ ውስጥ ገብተናል፡፡ ይህ ሊቆምና ቋንቋዎቻችን በዕቅድ ሊያድጉና ጥቅም ላይ ሊውሉ ይገባል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
የአማርኛ ቋንቋ የሀገሪቱ የስራ ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ክልሎች በፍፁም ጥላቻ እንዲመለከቱትና እንዲሁም ክፍል ውስጥ ገብተው የመማርን መብት ለተወላጆች ብቻ ትቻለሁ በማለት የአማርኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ፤ በትግራይ ፤ በኦሮምያና ደቡብ ክልሎች ክፍት እንደሚሆኑ ታዉቋል። ተማሪዎች በቋንቋ ትምህርት በሚመዱበበት ወቅትም በአማርኛ ቋንቋ የሚሰጡ ደጋፊ ትምህርቶችን ላለመማር አሰጣ አገባ እንደሚገቡ ታውቋል፡፡በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በቤንሻንጉል እና ሶማሌ ክልሎች የክልሎቹን ቋንቋ የማይናገሩ ተማሪዎች ተመርቀው ስራ ለማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ከአማራ ክልል የሚመጡ ተማሪዎች ከክልላቸው፣ ከአዲስ አበባ እና ከደቡብ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች ተቀጥረው ለመስራት እየተቸገሩ ነው።አንዳንድ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት ካልሆነ በስተቀር የአማራ ክልል ተማሪዎች ስራ ለመያዝ እንደሚቸገሩ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል። በሌላ በኩል ግን አማርኛ የሚችል የማንኛውም ክልል ተወላጅ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ስራ የመያዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

Sunday, October 13, 2013

በጎንደር ከተማ ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት ሞተው መገኘታቸው ከቦታው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል፣



October 13, 2013

በደረሰን ዘገባ መሰረት በጎንደር ከተማ በተለምዶ አራዳ አየተባለ በሚጠራው አክሱም ሆቴል አከባቢ መስከረም 26,2006 ዓ/ም ሌሊት ገዳያቸው ያልታወቁ ምክትል ሳጅን ይፍጠር ዓሊና ምክትል ሳጅን ደምመላሽ ይርዳው የተባሉ ሁለት የፌደራ ፖሊስ አባላት ሞተው ተገኝተዋል፣ ከሟቸቹ አንዱ በጩቤ ተወግቶ የተገደለ ሲሆን በሁለተኛው ላይ በዓይን የሚታይ አካላዊ ጉዳት አልነበረውም፣ ታጥቀውት የነበረውንም ትጥቅ በገዳዮቹ መወሰዱን ቷውቋል፣ በስርዓቱ የፌደራል ፖሊስ አባላት የሚደርሰው ጥቃት በሁሉም የሃገሪቱ ከተሞች የሚታይ ሲሆን በጎንደር ከተማ በሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት የደረሰውን ግድያ በIህአዴግ ስርዓት በተማረሩ የስርዓቱ ኗሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አይቀርም የሚል ጥርጣሬ በከተማዋ በሰፊው ይወራል::

Source : TPDM

ETV በቦሌ አዲስ አበባ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን ዘገበ

ዘገባው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት የተቀነባበረ ይሁን አይሁን በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠ የETV ዘገባ እንደወረደ 
እሁድ 3 2006 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የቤት ቁጥር 2333 ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሁለት ግለሰቦች ተከራይተው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ የፈንጂ ፍንዳታ መድረሱን የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ ጸረ ሽብር ሀይል ገለጸ፡፡
በፈንጂ ፍንዳታው ሁለቱ ግለሰቦች ህይወታቸው አልፏል፡፡
ጉዳዩን እያጣራ መሆኑን የገለጸው ግብረሀይሉ በምርመራ የደረሰበትን ውጤትም በቅርቡ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል፡፡
ህብረተሰቡ ቤት እና መኪናዎችን በሚያከራይበት ወቅት የተከራዮችን ማንነት ከማወቁም ባሻገር ለፖሊስ እና ለጸጥታ ሀይሎች ማሳወቅ እንዳለበት ግብረሀይሉ አሳስቧል፡፡

የኢህአዴግ አፈና አሁንም እንደቀጠለ ነው!! (ጥቅምት 2 ቀን 2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት)

ሰማያዊ ፓርቲ ለጽ/ቤት መጠቀሚያ ተከራይቶ ነበረውን ቢሮ በግድ ካልወጣችሁ ሲሉ ከነበሩት የጉለሌ ክ/ከተማና ወረዳ 03 ካድሬዎች መካከል በተነሳው ውዝግብ መፍትሄ ለማፈላለግ መሀከል የገባው የመነን አካባቢ ፖሊስ በውይይት ለመፍታት ሁለቱም አካላት ከቤቱ እንዲወጡና ፖሊስ ቤቱን እንዲጠብቅ፤ በቀጣዩ ቀን ለመነጋገር ስምምነት ተይዞ የፓርቲው አባላት ወደቤታቸው ለመሄድ ከጽ/ቤቱ ለቀው ቢሄዱም ከመንገድ ላይ
1.ወ/ት ሀና ዋለልኝ (የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ)
2.አቶ ዮናስ ከድር (የምክር ቤት አባል)
3.ወ/ት እየሩስ ተስፋው
4.አቶ ዮናታን ተስፋዬ
5.አቶ አቤል ኤፍሬም
6.አቶ አህመድ መሀመድ
7አቶ እያስፔድ ተስፋዬ
የአራዳ ክ/ከተማ ፖሊስና የደህንነት አካላት ወደ ጃልሜዳ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸው አሁን በደረሰን መረጃ ማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ በፊት እንደሚታወሰው የጃልሜዳ አካባቢ ፖሊስ የፓርቲውን አባላት እያሰረ ይደበድብ እንደነበረ ፤ አሁንም ከአንድ ሰአት በላይ አባሎቹን ምን እያደረጋቸው እንደሆነ ማወቅ አለመቻሉ እየተደበደቡ ይሁን? የሚለውን ስጋት በከፍተኛ ሁኔታ አጭሯል፡፡

Monday, October 7, 2013

በጣሊያኑ የባህር አደጋ የሞቱት የ153 የኢትዮጵያውያን እና የኤርትራውያን ስም ዝርዝር

italy
ሰሞኑን ከሊቢያ ተነስተው በጣሊያን ባህር አቅራቢያ ባህር ውስጥ ጠልቀው ከሞቱት ወገኖች ውስጥ በተለያዩ ሚዲያዎች የኤርትራ ስደተኞች ብቻ እንደሞቱ እየተዘገበ ነው። ዘ-ሐበሻ ግን የኤርትራ ስደተኞች መባሉን አታምንብተም። የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሔኖክ ዓለማየሁ በሊቢያ ስደት ውስጥ ያሳለፈ በመሆኑና ወደጣሊያንም በባህር ለመሻገር ሞክሮ በእስር ምክንያት ሕይወቱ በመትረፉ ዛሬ የኤርትራ ስደተኞች ብቻ ሕይወታቸው እንዳለፈ ተደርጎ መወራቱን አይቀበለውም። በሊቢያ ቤንጋዚ፣ ትሪፖሊ፣ ኩፍራ፣ ኢጅዳቢያና ሌሎችም እስር ቤቶች በርካታ ከምስራቅ አፍሪካ ወደ ጣሊያን ለመሰደድ ሄደው የታሰሩ ሰዎች ከዘ-ሐበሻ አዘጋጅ ጋር የታሰሩ ነበሩ። እነዚህ ዜጎች በተለይም ኢትዮጵያውያኑ እስር ቤት ሲገቡ ዜግነታቸውን ‘ኤርትራዊ እንደሆኑ እንዲናገሩ” አሻጋሪዎች ይነግሯቸዋል። ምክንያታቸውም የሊቢያ መንግስት እስር ቤት ውስጥ ኢትዮጵያዊ ነኝ ያለን ወደ አዲስ አበባ ስለሚሸኘው፤ ኤርትራዊ ነኝ የሚል ግን ወደ አስመራ ስለማይላክ ሁሉም ኢትዮጵያዊም ኤርትራዊም “ኤርትራዊ ነኝ” ብሎ ነው የሚገልጸው። አሁንም የሆነው ያ ነው። ኤርትራዊያን ናቸው ከተባሉት ውስጥ አብዛኛው ኢትዮጵያውያንም ጭምር ናቸው በሚል ዘ-ሐበሻ ታምናለች።
የሞቱትን ነብሳቸውን ይማረው፡ የሟቾች ዝርዝር የሚከተለው ነው፡

ኤርትራ በኢትዮጲያ መከላከያና ደህንነት ውስጥ ሰላዮችን ማሰማራቷን ኢትዮጲያ አመነች፥ ኢሳት ዜና

October 4, 2013
The charges under the files Fikru Abebe Haile, Tesfu Abate Abyneh, Mohmamed Umer Mohammed, Tamene  Tememte Zewde and Zerfu Melka, members of the Ethiopian Defense Forces, and accused of spying for Eritrea, reads that theEthiopian government has admitted that it has been infiltrated by the Eritrean IntelNetwork built between Addis Abeba, Borena and Nairobi, Kenya, ESAT has reported tonight.
The dossier that ESAT has accessed also states that Getachew Assefa, Head of the Ethiopian Intel, had told Intel members on a February 26, 2012 meeting that they had collected public opinion if they should go to war with Eritrea and the public’s response was against the idea. The details of this meeting were sent to Eritrea.
ESAT also reported that the dossier shows that the Ethiopian government has no interest of going into war with Eritrea but wanted to wipe out Ethiopian rebels that came from Eritrea through the North Western border of EthiopiaHumera and decided to weaken local opposition parties before the next election, 2015.
Listen to ESAT’s extended reportage here